Monday 29 April 2013

በሳንድያጎ የወያኔዎች ስብሰባ ሳይጀመር ተበተነ


በሳንዲያጎ የወያኔ አምባሳደር ይገኝበታል ተብሎ በአባይ ግድብ ስም ቦንድ ለመሸጥ የተጠራው ስብሰባ በኢትዮጵያውያን ተቃውሞ እንዲቋረጥ ሆንዋል።

Ethiopians in San Diego Protest April 28, 2013
በቁጥር ከሁለት መቶ በላይ የተቆጡና በርካታ መፈክሮችን ያነገቡ ኢትዮጵያውያን ስብሰባው በሚደረግበት አዳራሽ የተገኙት ቀደም ብለው ነበር።
TV channels covering Ethiopians demo. in San Diego
በርካታ ታዋቂ ሚድያዎች በቦታው ተገኝተው የተቃውሞዉን ትዕይንት የዘገቡ ሲሆን የቴሌቪዥን ጣብያዎች ዜናውን ማምሻው ላይ ለቀውታል።
ወያኔዎቹ በሌሎች ቦታዎች የገጠማቸውን ከግምት አስገብተው 3 ሰዎች በር ላይ አቁመው የራሳቸውን ሰዎች ብቻ መርጠው ለማስገባት ያደረጉት ሙከራ አልተሳካም።

ስብሰባው ሲጀመር የወያኔዎቹ ቁጥር ከ20 በታች ሲሆን ኢትዮጵያውያኑ ከሁለት መቶ በላይ ነበሩ።
ነገር አሳምራለሁ ብሎ ስብሰባውን እንግሊዝኛ ቋንቋ በመናገር የጀመረው የወያኔ ተወካይ በጥዋቱ ነበር ተቃውሞ የገጠመው፣ ኢትዮጵያውያኑ “እኛ ኢትዮጵያውያን ነን በቋንቋችን ተናገር” ብለው አስቆሙት። ተወካዩ ንግግሩን በአማርኛ ቀጠለ “እኛና እናንተ…” ብሎ ሊቀጥል ሲል አሁንም ከባድ ተቃውሞ ገጠመው “እናንተ እነማን ናችሁ? እኛስ ማን ነን? አትከፋፍለን እኛ አንድ ነን” አሉት።

No comments:

Post a Comment