Thursday 5 September 2013

አወዛጋቢው የጊቤ ግድቦች ጉዳይ


በየዓመቱ ከ 11 በመቶ በላይ ዕድገት እያስመዘገብኩ ነው የሚለው የኢትዮጵያ መንግሥት የኃይል ፍላጎቱን ለማሙዋላት በስፋት ከተያያዛቸው ፕሮጀክቶች መካከል ኣንዱ የጊቤ ወንዝን ተከትለው የሚገነቡት የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ፕሮጀክቶች ሲሆኑ
ከተለያዩ ወገኖች ማለት ይቻላል ተቃውሞ የገጠማቸው ታዲያ ገና ከጅምሩ ነበር። የውጪ ኃይሎችን ጨምሮ በተለይ ከመንግሥት ፈንጠር ያሉ በርካታ የዘርፉ ባለሙያዎች የግድቦቹ ግንባታ ፣ በቂ ጥናት ያልተካሔደባቸው እና ከኣካባቢ ጥበቃ አንፃርም ጥንቃቄ ዬጎደላቸው ናቸው ሲሉ ይከራከራሉ።
ሌላው ኣወዛጋቢ ጎኑ ደግሞ ከሥፍራው ስለሚፋናቀሉት የኣካባቢው ህብረተሰብ ዕጣ -ፈንታ ሲሆን ፣ ኣንዳንድ የዳውሮ ብሔረሰብ ኣባላት እንዲያውም ፕሮጀክቱ የብሔረሰቡን ታሪካዊ ኣሻራዎች ጭምር የሚያጠፋ አደገኛ ክሥተት ነው እስከማለት ነው የሚደርሱት።
ጃፈር አሊ 
ተክሌ የኋላ

No comments:

Post a Comment