Saturday 21 September 2013

የአቶ ቡልቻ መጽሐፍ ለንባብ በቃ

የአቶ ቡልቻ መጽሐፍ  ለንባብ በቃ
“ህይወቴ እና ለኦሮሞ እና ለሌሎችም የኢትዮጵያ ህዝቦች ያለኝ ራዕይ” በሚል ርዕስ በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀው የአቶ ቡልቻ ደመቅሳ መጽሐፍ በአሜሪካ ታትሞ በውጭ አገራት ለገበያ ቀረበ፡፡ መፅሃፉ አቶ ቡልቻ ከተወለዱባት የቦጂ በርመጂ ወረዳ ጀምሮ ከኦፌዴን ሊቀመንበርነት እስከለቀቁበት ጊዜ ድረስ ያሳለፉትን የትምህርት፣ የስራ እና የፖለቲካ ህይወት ይዳስሳል፡፡ ዘመናዊ ትምህርት ለመማር ያደረጓቸውን እልህ አስጨራሽ ሙከራዎች፣ ከአሜሪካን በኢኮኖሚክስ ተመርቀው ከመጡ በኋላ በገንዘብ ሚኒስቴር ውስጥ በምክትል ሚኒስትር ማዕረግ ባገለገሉባቸው አመታት ያጋጠሟቸውን ውጣ ውረዶች፣ በአለም ባንክ የኢትዮጵያ ተወካይ በመሆን እንዲሁም በዩኤንዲፒ ስለሠሯቸው ስራዎች በመጽሐፋቸው ተርከዋል፡፡

የኦሮሞ ህዝብን ጥያቄ አንስተው በፖለቲካው መስክ ስላደረጉት ተሳትፎ የፃፉት አቶ ቡልቻ፤ አዋሽ ባንክን ለመመስረት ያደረጉትን አስተዋጽኦና በባንኩ ውስጥ የተፈጠረውን አለመግባባትም በስፋት ዳስሰዋል፡፡ መጽሐፉ 180 ገፆች ያሉትና በ20 ምዕራፎች የተከፋፈለ ሲሆን በኦሮሚኛ እና በአማርኛ ቋንቋዎች ተተርጉሞ ለአገር ውስጥ ገበያ እንደሚቀርብ አቶ ቡልቻ ደመቅሳ ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡
http://www.addisadmassnews.com

No comments:

Post a Comment