የፈረንሳዩ ዜና አገልግሎት አዣንስ ፍራንስ ፕሬስ እንደዘገበዉ ግን የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት በኢትዮጵያ ቋንቋዎች ሳይሆን በፈረንሳይኛ፥ በእንግሊዝኛ ወይም በሌላ የአዉሮጳ ቋንቋ ለሚዘግቡት አልጠፉም።
መፈክሩ ባደባባይ ተነገበ፥ ተቀነቀነም።አዲስ አበባ ትናንት።ጩኸቱም ቀጠለ።ሰሚ-ያገኝ ይሆን?
«የታገተ ወይም በቁጥጥር ሥር የዋለ አንድም ሰዉ አላዉቅም።» አቶ ሪድዋን ሁሴን የኢትዮጵያ የኮሚንኬሽን ጉዳይ ሚንስትር ለአዣንስ ፍራንስ ፕረስ ትናንት እንደነገሩት።
አቶ ግርማ ሰይፉ የምክር ቤት እንደራሴና የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር።የትናንቱ የአዲስ አበባ የተቃዉሞ ሠልፍ መነሻ፥ የመንግሥት አፀፋ ማጣቃሻ፥ የኢትዮጵያ ፖለቲካዊ እዉነትና ሒደት መድረሻችን ነዉ-ላፍታ አብራችሁኝ ቆዩ።
መግባባት ቢቀር ለመቀራረብ ከቁጥር የቀለለ ነገር በርግጥ የለም።ትናንት ለተቃዉሞ ሠልፍ አደባባይ የወጣዉ ሕዝብ ቁጥር ሥንትነት ግን የሰልፉ አደራጆችንና የመንግሥትን ሹማምንት ከሚገመተዉ በላይ ነዉ-ያራራቀዉ።
«የታገተ ወይም በቁጥጥር ሥር የዋለ አንድም ሰዉ አላዉቅም።» አቶ ሪድዋን ሁሴን የኢትዮጵያ የኮሚንኬሽን ጉዳይ ሚንስትር ለአዣንስ ፍራንስ ፕረስ ትናንት እንደነገሩት።
አቶ ግርማ ሰይፉ የምክር ቤት እንደራሴና የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር።የትናንቱ የአዲስ አበባ የተቃዉሞ ሠልፍ መነሻ፥ የመንግሥት አፀፋ ማጣቃሻ፥ የኢትዮጵያ ፖለቲካዊ እዉነትና ሒደት መድረሻችን ነዉ-ላፍታ አብራችሁኝ ቆዩ።
መግባባት ቢቀር ለመቀራረብ ከቁጥር የቀለለ ነገር በርግጥ የለም።ትናንት ለተቃዉሞ ሠልፍ አደባባይ የወጣዉ ሕዝብ ቁጥር ሥንትነት ግን የሰልፉ አደራጆችንና የመንግሥትን ሹማምንት ከሚገመተዉ በላይ ነዉ-ያራራቀዉ።