Monday 30 September 2013

ኢትዮጵያ፤ የተቃዉሞ ሠልፍና እንቅፋቱ

የፈረንሳዩ ዜና አገልግሎት አዣንስ ፍራንስ ፕሬስ እንደዘገበዉ ግን የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት በኢትዮጵያ ቋንቋዎች ሳይሆን በፈረንሳይኛ፥ በእንግሊዝኛ ወይም በሌላ የአዉሮጳ ቋንቋ ለሚዘግቡት አልጠፉም።


መፈክሩ ባደባባይ ተነገበ፥ ተቀነቀነም።አዲስ አበባ ትናንት።ጩኸቱም ቀጠለ።ሰሚ-ያገኝ ይሆን?


«የታገተ ወይም በቁጥጥር ሥር የዋለ አንድም ሰዉ አላዉቅም።» አቶ ሪድዋን ሁሴን የኢትዮጵያ የኮሚንኬሽን ጉዳይ ሚንስትር ለአዣንስ ፍራንስ ፕረስ ትናንት እንደነገሩት።


አቶ ግርማ ሰይፉ የምክር ቤት እንደራሴና የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር።የትናንቱ የአዲስ አበባ የተቃዉሞ ሠልፍ መነሻ፥ የመንግሥት አፀፋ ማጣቃሻ፥ የኢትዮጵያ ፖለቲካዊ እዉነትና ሒደት መድረሻችን ነዉ-ላፍታ አብራችሁኝ ቆዩ።
መግባባት ቢቀር ለመቀራረብ ከቁጥር የቀለለ ነገር በርግጥ የለም።ትናንት ለተቃዉሞ ሠልፍ አደባባይ የወጣዉ ሕዝብ ቁጥር ሥንትነት ግን የሰልፉ አደራጆችንና የመንግሥትን ሹማምንት ከሚገመተዉ በላይ ነዉ-ያራራቀዉ።

Saturday 28 September 2013

አቶ ግርማ ሠይፉ እና የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራር አባላት ተይዘው ተለቀቁ

የአንድነት ለፍትሕና ለዴሞክራሲ ፓርቲ ከፍተኛ የአመራር አባላት ዛሬ ለሦስት ሰዓት በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውለው መለቀቃቸውን ገልፀዋል፡፡ግርማ ሠይፉ - እንደራሴ


ከተያዙት መካከል አንዱ “እጃቸው ያለመያዝ መብት” ያላቸው እንደራሴ የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር ግርማ ሠይፉ እንደሆነም ታውቋል፡፡

በቁጥጥር ሥር ውለው ከነበሩት ሌሎች የፓርቲው አመራር አባላት መካከል ሊቀመንበሩ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ፣ ዋና ፀሐፊው አቶ አሥራት ጣሴ፣ የሥራ አመራር ኮሚቴው አባልና የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው አቶ ዳንኤል ተፈራና ምክትላቸው አቶ ሃብታሙ አያሌው፣ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴው አባላት አቶ ተክሌ በቀለ፣ አቶ ስዩም መንገሻ እና አቶ ሺመልስ ሃብቴ፣ የፓርቲው ብሔራዊ ምክር ቤት አፈጉባዔ አቶ ዘካርያስ የማነብርሃን፤ እንደሁም ሰላሣ ሦስቱ እየተባሉ ከሚጠሩት ስብስብ መካከል የሆኑ ሌሎችም ፓርቲዎች መሪዎች እንደሚገኙበት ታውቋል፡፡

Friday 27 September 2013

ስበር ዜና – አንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችና አባላት ታሰሩ!

September 27, 2013


የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ዛሬም ታግተው ወደ አራዳ ፓሊስ ጣቢያ ተወስደዋል፡፡ አብረዋቸው የታሰዩት አመራሮችና አባላት እንደሚከተለው እንዘረዝራለን !Millions of voices for freedom - UDJ
በፖለስ የታሰሩ አመራሮችና አባላት በከፊል
ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ – የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር
የተከበሩ ግርማ ሰይፉ – የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር
አቶ ስዩም መንገሻ – የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ
አቶ ዳንኤል ተፈራ – የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ
አቶ አስራት ጣሴ – ዋና ጸሃፊ
አቶ ተክሌ በቀለ – የፋይናንስ ጉዳይ ኃላፊ
አቶ ሽመልስ ሃብቴ – የማህበራዊ ጉዳይ ኃላፊ
አቶ ሃብታሙ አያሌው – የህዝብ ግንኙነት ም/ኃላፊ
አቶ ብሩ በርመጂ – የብሔራዊ ምክር ቤት አባል
አቶ አበበ አካሉ – የብሔራዊ ምክር ቤት አባል
አቶ እንግዳ ወ/ፃዲቅ – የብሔራዊ ምክር ቤት አባል
አቶ አለባቸው ነጋሽ – አባል
አቶ መካንንት ብርሃኑ – አባል
አቶ እንዳልካቸው ባዩ – አባል
አቶ ብስራት ተሰማ – አባል
አቶ ወንደሰን ክንፉ – አባል
አቶ ኃይሉ ግዛው – አባል
አቶ ደረጀ ጣሰው – አባል
አቶ ገዛህኝ – አባል
አቶ ባዩ ተስፋዬ – አባል
አቶ ወርቁ – አባል

http://ecadforum.com/Amharic/

“ወሲባዊ ጂሃድ (ጂሃድ አል-ኒቃ)” በሶሪያ! ሳዑዲ ሞት የፈረደችባቸውን ወደ ሶሪያ አዝምታለች


tunisian girls


የቱኒዚያ ሴቶችና ልጃገረዶች በሶሪያ የአሳድን መንግሥት እየተፋለሙ ከሚገኙት እስላማዊ አማጺያን ጋር “ወሲባዊ ጂሃድ” በመፈጸም በጦርነቱ ላይ ተሳትፏቸውን እየገለጹ መሆናቸው ተነገረ፡፡ በሌላ በኩል በዚሁ ጦርነት ላይ በሳውዲ አረቢያ የሞት ፍርድ የተበየነባቸው ወንጀለኞች እንዲሳተፉ እየተላኩ መሆናቸው ተረጋገጠ፡፡
በያዝነው የመስከረም ወር መጀመሪያ አካባቢ የቱኒዚያው የአገር ውስጥ ሚኒስትር ሎትፊ ቢን ጄዱ በአገሪቱ ፓርላማ ፊት ቀርበው እንደተናገሩት በጦርነቱ ከፍተኛ መስዋዕትነት እየከፈሉ ለሚገኙት ተዋጊዎች ማደፋፈሪያ እንዲሆንና በትግሉ የነርሱንም ድርሻ ለመወጣት የቱኒዚያ ሴቶችና ልጃገረዶች ራሳቸውን በ“ወሲባዊ ጂሃድ” በመስጠት ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡

Thursday 26 September 2013

No Human Rights = No Development

September 26, 2013

Oakland Institute and the Housing and Land Rights Network Submit Human Rights Report on Ethiopia to the United Nations

OAKLAND CA- In a report submitted to the UN Human Rights Council’s Universal Periodic Review (UPR) on September 15, 2013, the Oakland Institute and the Housing and Land Rights Network outlined the human rights and international law violations perpetrated by the government of Ethiopia in the name of country’s development strategy.
Drawing clear links between recorded testimonies on the ground and breaches of specific international covenants and articles in Ethiopia’s constitution, the joint submission to the UN Human Rights Council also responds to Ethiopia’s draft National Human Rights Action Plan for 2013-2015. “Rather than working to build a development strategy grounded in human rights, the Ethiopian government is attempting to hoodwink its human rights record, leaving unmentioned its villagization program and the Anti-Terrorism Proclamation-both used by the government as significant justifications for forced resettlement, arbitrary detentions, and politically motivated arrests,” said Anuradha Mittal, Executive Director of the Oakland Institute.

ኬንያና እንግሊዛዊቷ አሸባሪ፤

ኬንያ፤ በመዲናዋ በናይሮቢ ዌስትጌት በተባለው ግዙፍ የገበያ ህንጻ ውስጥ ፣ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ፣ በሶማልያው አሸባብየአሸባሪዎች ቡድን፤ ቢያንስ72 ሰዎች ከተገደሉ ወዲህ ፣የ 67 ቱ ሰለባዎች የቀብር ሥነ ሥርዓት ተፈጽሟል ። የ3 ቀን የኀዘን ጊዜም ታውጆ ተግባራዊ በመሆን

ላይ ሳለ፣የዩናይትድ እስቴትስ፤ የብሪታንያ፤ የአሥራኤልና የሌሎችም ጠበብት ከኬንያ የምርመራ ጠበብትጋር በመተባበር፤ አደጋው እንዴትሊሠነዘር እንደቻለ በማጣራት ላይ መሆናቸውታውቋል። 40 ሚሊዮን ኑዋሪዎች ባሏት ኬንያ የሙስሊሞች ቁጥር 10 ከመቶ ገደማ ሲሆን፣ ተገቢ ቁጥጥር በማይደረግበት ድንበር፤ ሠርገው የሚገቡ የአሸባብ ታጣቂዎች ከአንዳንድ ኬንያውያን የእምነት ተጋሪዎቻቸው ድጋፍ እንዳልተለያቸው ተነግሯል። አሸባብ ፤ ሶማሌዎችን ብቻ ሳይሆን የተለያዩ ሃገራት ተወላጆችንም ማሰለፉ ይነገርለታል። ከእነዚህም አንዷ ሳምንታ የተባለችው እንግሊዛዊት መሆኗ ታውቋል። ይህች ሴትዮ እንዴት በሽብር ተግባር ለመሰማራት ተነሳሳች? የለንደኑን ዘጋቢአችንን ድል ነሣ ጌታነህን በስልክ ጠይቄው ነበር።
audio ለመስማት ሊንኩን ይቻኑት

የመንግስት የደህንነት መስሪያ ቤት ከወልድያ ሙስሊም ተማሪዎች አመጽ ጀርባ ሼክ ሙሀመድ አላሙዲን አሉበት አለ

መስከረም ፲፮(አስራ ስድስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መንግስት ፣ “ኢህአዴግን የፈተነ ወሳኝ ክስተት” በማለት የገለጸውን የሙስሊሞች እንቅስቃሴ አልሻባብ፣ አልቃይዳ ፣ ግንቦት ሰባት ፣ እና የኤርትራ መንግስት እንደሚደግፉት በተደጋጋሚ በመገናኛ ብዙሀን ቢገልጽም፣ ለኢሳት የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው ከሆነ ደግሞ የደህንነት ሀይሎች ቱጃሩን ሼክ ሙሀመድ ሁሴን አላሙዲንን ከእንቅስቃሴው ጀርባ እንዳሉበት የሚጠቁም መረጃ ለመንግስት ባለስልጣናት ማቅረቡ ታውቋል።

በቅርቡ በወልድያ ከተማ የወልድያ ሙስሊም ተማሪዎች ባነሱት አመጽ መንገድ ዘግተው ወደ ላሊበላ ፤ ሰቆጣ ፣ ደሴ እና አዲስ አበባ የሚደረጉ የትራንስፖርት ጉዞዎች እንዲስተጓጎሉ ማድረጋቸው ይታወሳል፡፡
ከዚሁ ጋር በተያያዘ አመጹን አነሳስታችሁዋል የተባሉ 13 ታዳጊ ወጣቶች በእስር ላይ ይገኛሉ፡፡ የደህነነት ሐይሎች አጣራነው ባሉት መረጃ አመጹን ሼክ አላሙዲን ከጀርባ ሆነው ደግፈውታል።
የኢህአዴግ አመራር እና የፌደራል ፖሊስ የጋራ የጸረ ሽብር ግብረ ሐይል በጉዳዩ ዙሪያ በሰፊው ውይይት ካደረጉበት በኃላ ፣ በባለሀብቱ ላይ እርምጃ ለመውሰድ ባይቻልም በወዳጆቻቸው  በኩል ምክር አንዲሰጣቸው በአቶ በረከት ስምኦን የሚመራ አንድ ቡድን መዋቀሩን ለማወቅ የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

የሀይማኖት አቋም የእድገት መመዘኛ መስፈርት እንዲሆን ተወሰነ የሀይማኖት አቋም የእድገት መመዘኛ መስፈርት እንዲሆን ተወሰነ


Bereket_simon

መስከረም ፲፭(አስራ አምስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአቶ በረከት ስምኦን በተመራው የኢህአዴግ ማእከላዊ ኮሚቴ ውይይት ላይ ፣ የሀይማኖት አክራሪነት ከምርጫ 97 ቀጥሎ ከፍተኛ ፈታኝ አደጋ እንደሆነ ከተገለጸና ውይይት ከተካሄደ በሁዋላ የአገሪቱ ሲቪል ሰርቪስ የሀይማኖት ጉዳይን እንደ አንድ የእድገት መመዘኛ መስፈረት እንዲተገብር ስምምነት ላይ ተደርሷል።
በጉባኤው ላይ የሐይማኖት አክራሪነት የመንግስትን ተቋም በማፈራረስ እና ተከታዮቹ ነፍጥ አንስተው መስዋእት እንዲሆኑ በማነሳሳት ከፍተኛ የሆነ አደጋ ይፈጥራል ሲሉ አቶ በረከት ተናግረዋል፡
በኢትዮጵያ ታሪክ በዩዲት ጉዲት እና በግራኝ አህመድ ዘመን በከፍተኛ ሁኔታ የደረሰውን የመንግስት ውድመት ዳግመኛ ሊፈጥር የሚችል አዝማሚያ አለው ሲሉ የተናገሩት አቶ በረከት፣ ይህንን በተማረው ህብረተሰብ እየታየ ያለውን በመንግስት ላይ ሊፈጠር የሚችለውን አደጋ ለመቋቋም ያስችል ዘንድ፣ በማንኛውም ሁኔታ በህዝብና በመንግስት ተቋማት ውስጥ መዝሙር ማዳመጥ ፤ የሐይማኖትን መልእክት የሚያንፀባርቁ ማንኛውንም ሃሳብ መለጠፍ ፤ መስበክ፤ የሞባይ መጥሪያ ድምጽ ማድረግ ፈጽሞ መከልከሉን ገልጸዋል።

Wednesday 25 September 2013

ወታደራዊ መኮንኖች የደሞዝ ይጨመርልን ጥያቄ አቀረቡ

መስከረም ፲፭(አስራ አምስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች ካለፉት 8 ቀናት ጀምሮ ስብሰባ ላይ ሲሆኑ የደሞዝ ጭማሪ ጥያቄ ዋነኛው የመነጋገሪያ አጀንዳ መሆኑ ታውቋል።

ከመቶ አለቃ በላይ ማእረግ ያላቸው ወታደራዊ መኮንኖች ስብሰባዎችን እያካሄዱ ያሉት የጄኔራሎች ስብሰባ ከወር በፊት መጠናቀቁን ተከትሎ ነው። በጄኔራሎቹ ስብሰባ ላይ ለሰራዊቱ የደሞዝ ጭማሪ ጥያቄ ተነስቶ የነበረ ቢሆንም፣ “ሰራዊቱ አሁን የሚያገኘው ደሞዝ ለኑሮው በቂ ነው” የሚል መልስ ከሰራዊቱ ዋና አዛዦች ተሰጥቷል።  በተሰጠው መልስ የተበሳጩት  ጄኔራል ሰአረ መኮንን ስብሰባ ረግጠው ወጥተው እንደነበር ታውቋል። ጄኔራሉን ለማረጋጋት ከፍተኛ ጥረት ተደርጎ እንደነበርም የደረሰን መረጃ ያመለክታል። ጄኔራል ሰአረ ለሰራዊቱ ደሞዝ እንዲጨመር አቋም ከያዙት ከፍተኛ መኮንኖች መካከል አንዱ ናቸው።
ሰሞኑን በመካሄድ ላይ ባለው ከጄኔራል በታች ማእረግ ባላቸው መኮንኖች ስብሰባም   የደሞዝ ጭማሪና የኑሮ ውድነት ዋና አጅንዳ ሆኖ ቀርቧል።
በምስራቅ አካባቢ ባለው እዝ አንዳንድ መኮንኖች ” እኛ ቤተሰቦቻችንን ምግብ አብልተን ለማኖር አልቻልንም፣ እናንተ በሙስና በዘረፋችሁት ገንዘብ ልጆቻችሁን ውጭ አገር ልካችሁ ታስተምራላችሁ” በሚል አለቆቻቸውን በድፍረት መተቸታቸውን የውስጥ ምንጮች ገልጸዋል።   መኮንኖች ያቀረቡትን ጥያቄ የመደረክ መሪዎች ለመመለስ ሲቸገሩ ታይቷል።

የቀድሞው ፕሬዚዳንት የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ከእስር ተፈቱ

መስከረም ፲፭(አስራ አምስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ዶ/ር ነጋሶ  ዛሬ ከቀኑ 9 ሰአት ላይ ሽሮ ሜዳ በሚገኝ እስር ቤት ውስጥ እንዲታሰሩ መደረጉን  የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ  አቶ ዳንኤል ተፈራ ከገለጹ ከሰአታት በሁዋላ ፣ ሊቀመንበሩ ማምሻውን ተፈትተዋል።
አንድ ግለሰብ “የፓርቲው የሰላማዊ ሰልፍ የቅስቀሳ ግብረሀይል አባላት ያለፍላጎቴ ፎቶግራፍ አንስተውኛል” በሚል ክስ መመስረቱን ተከትሎ ፣ የቅስቀሳ አባላቱ መያዛቸውንና እነሱን ለማስፈታት ወደ ስፍራው ያቀኑት ዶ/ር ነጋሶ እንዲታሰሩ ተደርጎ የተያዙት እስረኞች እንዲለቀቁ” መደረጉን አቶ ዳንኤል ተናግረዋል።
አንድነት በመጪው እሁድ ለሚያደርገው የተቃውሞ ሰልፍ ከፍተኛ ቅስቀሳ በማድረግ ላይ ነው። ፓርቲው ሰልፉን በመስቀል አደባባይ እንዳያደርግ በአዲስ አበባ መስተዳድር መከልከሉን ተከትሎ በአማራጭነት ሌሎች አደባባዮችን ማቅረቡንም አቶ ዳንኤል አክለዋል
ተቃዋሚዎች ሕገመንግስታዊ መብታቸውን መሰረት በማድረግ ከምርጫ 97 በሁዋላ ባልታየ መልኩ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየጠሩት ያለውን ሰላማዊ ሰልፍ  ኢህአዴግን ስጋት ላይ ጥሎታል። ሰሞኑን በአዲስ አበባ እና በሌሎችም ከተሞች የሚደረጉ ሰልፎችን በተመለከተ አዲስ መመሪያ ማውጣቱ ይታወቃል።

ፖሊስ የቀድሞውን የኢትዮጵያ ፕሬዘዳንት ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳን አሰረ

              
የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ፕሬዘዳንት ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ የታሰሩ የፓርቲውን የቅስቀሳ ቡድን አባላት ለማስፈታት ወደ ጉለሌ ክፍለ ከተማ የሽሮ ሜዳ ፖሊስ ማዘዣ ጣብያ በማምራት ለፖሊሶቹ ‹‹ልጆቹ የፈጸሙት ህገ ወጥ ድርጊት የለም፣ሲቀሰቅሱ የነበሩትም እውቅና የተሰጠውን ሰላማዊ ሰልፍ ነው፡፡ቅስቀሳው ህገ ወጥ ነው የምትሉም ከሆነ እነርሱን የላኳቸው እኔ በመሆኔ እኔን ልታስሩኝ ትችላላችሁ ››ብለዋል፡፡
ፖሊስ የቀድሞውን የኢትዮጵያ ፕሬዘዳንት ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳን በማሰር ወጣቶቹን ለቅቋቸዋል፡፡


http://www.abugidainfo.com/amharic/index.php/12163

“ማኅበረ ቅዱሳን አክራሪ ሆኖ የገደለው ሰው የለም’ – ዲ/ን ዳንኤል ክብረት ምላሽ ሰጠ


የቀድሞው ጠቅላይ ሚ/ር መለስ ዜናዊ በፓርላማ ማህበረ ቅዱሳንን “አክራሪ” ሲሉ መግለጻቸው ይታወሳል። ከቅርብ ግዜ ወዲህ ደግሞ የአቶ ኃይለማርያም መንግስት በተለይ የጸረ ጽንፈኝነትን እና አክራሪነትን ለማጥፋት እታገላለሁ እያለ ባለበት ወቅት ማህበረ ቅዱሳንን ደግሞ አክራሪ ሲል መግለጹ ከፍተኛ ቁጣን መቀስቀሱ ይታወሳል። በአዲስ አበባ እየታተመች የምትወጣው እንቁ መጽሔት ሰሞኑን ዲ/ን ዳንኤል ክብረትን አነጋግራ ወጥታለች – በዚህ ጉዳይ። ዘ-ሐበሻ ይህን ቃለ ምልልስ እንደወረደ ለአንባቢ ግንዛቤ ሊሰጥ ይችላል በሚል መንፈስ አስተናገዳዋለች።
ዕንቁ፡- ጽንፈኝነት ምንድን ነው? አክራሪነትስ?
ዲ/ን ዳንኤል ክብረት፡- አንድን ነገር ወደ ጥግ ወይም ወደ መጨረሻው ጠርዝ ላይ መውሰድ ጽንፈኝነት ነው፡፡ በነገራችን ላይ፣ አክራሪነት ይሁን ጽንፈኝነት በጽንሰ ሐሳብ ደረጃ ብዙም ልዩነት ያላቸው ጉዳዮች አይደሉም ፡፡ ልዩነታቸው በአፈጻጸም ላይ ነው ፡፡ ጽንፈኞቹ ‹‹ይሄ እና ይሄ ብቻ!›› የማለት ጠባይ አላቸው፡፡ አክሪዎቹ ደግሞ ‹‹ይሄ እና ያ….. ካልሆነ እንዲህ እናደርጋለን›› ወደሚልና ወደ ተግባሩ ርምጃ የሚያዘሙት ናቸው፡፡ ጽንፈኝነት በየትኛውም ጠባይ ሊኖር ይችላል፡፡ በማንኛውም ጉዳይ በቅርብ ስትመጣ ለዘብተኝነት ፣ ወደ መሀል ሲሆን ወግ አጥባቂነት ፣ ወደ ዳር ሲኬድ ጽንፈኝነት ይኖራል፡፡ በባሕልም ቢኾን ለዘብተኛ ሰው አለ ፤ ማንኛውም ባህል ምንም የማይመስለው፡፡ ባህሉን የሚያጠብቅም አለ ፤ ‹‹ባሕሌን እወደዋለኹ፤ አከብረዋለኹ፤ ለምን ትነካብኛለህ? ለምንስ ትበርዘዋለህ? እንዲሁ ሳይበረዝና ሳይከለስ እንዲሁ እንዲኖርልኝ እፈልጋለኹ. . .›› ብሎ የሚያስብ ሰው አለ፡፡ ወደ ዳር ያለው ደግሞ ‹‹ከዚህ ውጭ ያለውን ፈጽሞ ማየትም ኾነ መስማት አልፈልግም!. . .›› ባይ ነው፡፡ የሌላውን ህልውና የሚክድ ነው፡፡ ይህ ለእኔ ተፈጥሯዊ ነው፡፡ ከባዱ ነገር አክራሪነት ነው፡፡ ወደ አክራሪነት ስትመጣ ‹‹ይሄኛውን ካልተቀበለ…›› ከሚል ይነሣና ርምጃ እስከ መውሰድ ጥግ ድረስ የሚሄድ ይሆናል፡፡

President’s office concludes a 400,000 birr house rent deal for outgoing President Girma

By Muluken Yewondwossen
Monday, 23 September 2013 13:05
Previous 530,000 birr deal annulled
The Office of the President has finally concluded a deal to rent a 400,000 birr per month residence for outgoing President Girma Woldegiorgis on Friday September 20, canceling previous plans to rent a fully furnished house from Elias Arega at 530,000 birr a month. The current house owned by Solomon Girma, businessman and owner of Mesale Bar and Restaurant, has been selected by the government to be the residence of President Girma, who has served in the position for the past 12 years after the first president, Negaso Gidada (PhD) resigned in 2001. In the past few months the president’s office, i.e. the Palace Administration, has been looking to rent a house for the outgoing president.

Woyane got it all wrong; it has no way out but the unconditional surrender for democratic rule

September 24, 2013

The Ethiopian regime seems to misunderstand what the people of Ethiopia are demanding. The sooner the regime gets it and surrender peacefully for democratic rule the better it would be. Playing hide-and-seek game isn’t going to do it.  Spewing empty ethnic and religious propaganda isn’t going to save it. Hiding behind corrupt investments and empty growth propaganda isn’t a substitute for freedom. Tormenting the population and jailing the innocent with empty bravado isn’t going to help it form its inevitable demise. Woyane and its stooges must appreciate the tolerance of our people and accept the illegitimacy of the ruling regime and live with it. Noting will change that reality. 
by Teshome Debalke
Stupidity is a virtue brought about by ignorance, empty self-worth and bravado; oftenexhibited in a circle of people in-and around tyrannies, gangs and rouge groups that rely on intimidation and brut force to sustain their existence.  Therefore, the Ethiopian ruling regime known for its stupidity and brutality on the top of its organized corruption has no qualm to remain on the bottom of the pits since it came to power. Its apologists aren’t far behind; not willing to rise up to the occasion when the rotten regime reduces them to impersonator beyond recognition.Hailemariam Desalegne, the Prime Minster appointed to replace Melse
When the self-declared minority regime implemented Apartheid to insure its survival it was bound to commit atrocities and corruption beyond an average tyranny. When the apologist lie through their teeth to cover up for its crimes it was clear illustration of how a confined ethnic audience can be manipulated to play on the bottom. Therefore, the Woyane regime has one thing going for it; a collection of ethnic yes-men clapping with one hand and stealing with the other to make enough noise for the world to believe there is something out of noting.

የሙስሊሞች ጉዳይ መፍትሔ ይሻል!


የናይሮቢው የዌስትጌት ሞል ጥቃት አሰቃቂ ነው። ግን ጥቃቱ ለኛ ኢትዮዽያውያን ምን ዓይነት ስሜት ፈጠረ? “የተለያየ ስሜት” እንበለው ላለመሳሳት። በዚህ ጉዳይ ኬንያና ኢትዮዽያ ይመሳሰላሉ እንዴ?

በኬንያ ግለሰቦች ንፁሃን ሰለማዊ ዜጎችን በገበያ ማእከል ያግዳሉ፣ ያሰቃያሉ፣ ይገድላሉ። በኢትዮዽያ ደግሞ የገዢው ፓርቲ ፖሊሶች ንፁሃን ሰለማዊ ዜጎችን በመስጂዶች ያግዳሉ፣ ያሰቃያሉ፣ ይገድላሉ። ስለዚህ በኬንያና በኢትዮዽያ ዉስጥ የሚፈፀሙ ድርጊቶች የሚመሳሰሉበት ነጥብ በሁለቱም ተጠቂዎቹ ሰለማዊና ንፁሃን ዜጎች መሆናቸው ነው። የሚለያዩበት ደግሞ በኬንያ ጥቃት የሚፈፅሙ ግለሰቦች ሲሆኑ በኢትዮዽያ ግን የመንግስት ሃይሎች ናቸው።

ይቅርታ!

በሁለቱም ሀገሮች የሚፈፀሙ ጥቃቶች ይመሳሰላሉ። በኬንያ ለተፈፀመ ድርጊት ሓላፊነት የወሰደ አልሸባብ አይደለምን? ስለዚህ በናይሮቢ የሽብር ተግባር የፈፀሙ ሃይሎች ግለሰቦች ሳይሆኑ ድርጅት ነው። ምክንያቱም ጥቃቱ የፈፀመው አልሸባብ ነው። አልሸባብ ደግሞ ድርጅት ነው። በኢትዮዽያ የሚፈፀመውም በገዢው ፓርቲ ነው። ገዢው ፓርቲ ድርጅት ነው። ስለዚህ በሁለቱም ሀገሮች የሚፈፀሙ ጥቃቶች በድርጅቶች የትፈፀሙ ናቸው። ስለዚህ ይመሳሰላሉ።

Tuesday 24 September 2013

Libya: Thousands of Refugees in Life-Threatening


HRLHA FineHRLHA Urgent Action
September 24, 2013
For Immediate Release
The Human Rights League of the Horn of Africa (HRLHA) has learnt through its correspondents that hundreds of thousands of refugees in Libya, most of whom were from the Horn of African countries such as Ethiopian and Eritrea, are in a very dangerous situation after they were evicted from their original refugee camps in Benghazi, Libya where they stayed for the past three years. The eviction took place following the infiltration and assault of the refugees by who were described as workers of the Libyan Red Crescent on the 13th of September, 2013. The assault included beating and stabbings by knives. Those who broke out of the shelters to run away from the assaults were met with Libyan armed forces that were stationed around the camps prior to the starting of the assault. Then, the refugees were forced out of the camp on allegations that they attempted to instigate disturbances in the city, and taken to remote area known as Alshatti.
According to HRLHA correspondents, about 500 refugees are now held in what was known to be a private detention centre in Alshatti located on Sahara Desert border with no adequate supply of basic necessities. HRLHA has also learnt that the very adverse weather condition at Alshatti has worsened the situation to the refugees. Even two expecting women who delivered after arriving in Alshatti and their newly born infants were not treated differently. The fact that the refugees are now held in isolation where they are not visited by international agencies like the UN High Commission for Refugees and the ICRC until this Urgent Action is documented,  as they used to when they were sheltered in Benghazi, added to the very unfriendly living condition has raised their frustrations. The refugees who were contacted by HRLHA also mention that there have been detachments and disconnections among refugees who had acquaintances and/or relationships with each other. Most of the refugees who were taken to Alshatti are originally from Ethiopia and Eritrea, HRLHA correspondents have added.

Azeb Mesfin arrest imminent


azeb_mesfinSeptember 24, 2013
Azeb Mesfin, the widow of Ethiopia’s deceased dictator, is facing multiple charges of corruption and her arrest is imminent unless she leaves the country, according to Ethiopian Review sources in Addis Ababa.
Political and business associates of Azeb Mesfin are dropping like flies. The biggest one to fall was Gebrewahid WoldeGiorgis, a senior official, who was charged with stealing over one hundred million Birr. Others are leaving the country with their families. Since May 2013, over 50 high profile TPLF officials and businessmen have been arrested on charges of corruption. All of them are associates and partners of Azeb.
Azeb, also known as, the Mother of Corruption, is currently being protected by Abay Woldu, chairman of the ruling Tigray People Liberation Front (TPLF), and Bereket Simon, former propaganda chief, but both Abay and Berket are being marginalized, and Abay is fighting to maintain his diminishing authority over TPLF.

A Journalist kidnapped, Threatened, and Beaten by Intelligence and Security Agents in Ethiopia

September 24, 2013

by BetreYacob
Ethiopian journalist Bisrat Woldemichael
Ethiopian journalist Bisrat Woldemichael
The Ethiopian journalist Bisrat Woldemichael was kidnapped, threatened, humiliated, and beaten by the Ethiopian intelligence and security agents on 28 August, 2013. He has reported this incident today to journalists.
Bisrat reported that the dreadful incident took place at Gotera, a place in the capital Addis Ababa as he was walking home from work. He said he was victimized for exercising his right to free expression in conjunction with the related right to press freedom.
Bisrat Woldemichael works for a magazine, Ebony, as Editor in Chief, and writes political articles on different Ethiopian private press outlets. He also blogs at  www.addismedia.wordpress.com andwww.ethiopiahot.wordpress.com. The journalist is known for his outspoken articles focused on the poor governance and pervasive human right violation, which are turning the oldest East African nation, Ethiopia, into a hell.
Violence against journalists is a common practice in Ethiopia, a country generally regarded as one of the most dangerous places to be a journalist. According to Amnesty International, during the past three years only, over 100 prominent journalists were brutally prosecuted on fabricated charges, and too many others were also subjected to harassment, intimidation, and other violence.

ዜና ከአዲስ አበባ – 15 የሚሆኑ የአንድነት ፓርቲ አባለት ዛሬ ህገወጥ እስር ተፈፀመባቸው፤ የአራት ኪሎን ህዝብ እናመሰግናለን – ፍኖተ ነጻነት


አንድነት ፓርቲ በመጪው እሁድ መስከረም 19 ከ33ቱ ፓርቲዎች ጋር ለሚያደርገው ሰላማዊ ሰልፍ የመኪና ላይ ቅስቀሳ ሲያደርጉ የነበሩ 15 አባላቱ ህገወጥ እስር ተፈፀመባቸው፡፡ አባላቱ ከስድስት ኪሎ ወደ አራት ኪሎ በሚወስደው ጎዳና በመኪና ላይ እየቀሰቀሱ ባለበት ወቅት ሚኒሊክ ት/ቤት ፊትለፊት የፖሊስና የደህንነት ኃይሎች የሚተላለፈውን መኪና መንገድ በመዝጋት ቅስቀሳውን አደናቅፈዋል፡፡
በስፍራው የነበሩ በርካታ ሰዎች “ቀስቃሾቹ ህጋዊ ወረቀት ይዘዋል፤ልቀቋቸው” በማለት ተቃውሞ አሰምተዋል ከአንድነት ፓርቲ ጎን እንደሚቆሙም ተናግረዋል፡፡ ፖሊስ 15 የሚሆኑትን የቅስቀሳ ቡድን አባላት ወደ ሁለተኛ ፖሊስ ጣቢያ ወስደዋቸዋል፡፡ የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች አባላቱ ወደ ታሰሩበት 2ኛ ፖሊስ ጣቢያ በመሄድ ረ/ኢ መንግስቱ ለማ የተባሉትን የፖሊስ ጣቢያው ኃላፊ የታሰሩት አባላት እንዲለቀቁ ጠይቀዋል፡፡ ኃላፊውም “ህጋዊ ሰልፍ እንደምታደርጉ እናውቃለን ይቀስቅሱ የሚል መመሪያ አልደረሰንም ብለዋል፡፡ አመራሮቹ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽነርንና የከተማዋን መስተዳድር ሃላፊዎች ለማነጋገር ተንቀሳቅሰዋል፡፡

ሙስሊም ወንድማማች ዕገዳ ተጣለበት

ውሳኔው የሙርሲን “ቅርንጫፍ” ድርጅቶችንም ይጨምራል

m b


የካይሮው አስቸኳይ ጉዳዮች ፍርድቤት የሙስሊም ወንድማማችን እና ከእርሱ ጋር ግንኙነት ያላቸውን መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን በሙሉ ከማንኛውም እንቅስቃሴ አገደ፡፡ የመካከለኛው ምስራቅ የዜና አገልግሎትን ጠቅሶ አልጃዚራ እንደገለጸው ዕገዳው መሐመድ ሙርሲ ይመሩት የነበረውን እና ከሙስሊም ወንድማማች ጋር የጠበቀ ግንኙነት ያለውን የእስላማዊው እንቅስቃሴ የፖለቲካ ክንፍ የነጻነትና ፍትሕ ፓርቲንም ሊጨምር ይችላል፡፡
በሕዝብ ድምጽ ሥልጣን የተረከቡትን መሐመድ ሙርሲ በመፈንቅለ መንግሥት ከሥልጣን ከተወገዱ በኋላ የሙስሊም ወንድማማች ደጋፊዎችና ከፍተኛ አመራሮች አሁንም እየታሰሩና እየተገደሉ ይገኛል፡፡
ከፖሊስና፣ ከደኅንነትና ከመፈንቅለ መንግሥቱ ደጋፊዎች ጋር የሚደረገው ውዝግብ ደም አፋሳሽ ከመሆን አልፎ በወንድማማቾቹ እንቅስቃሴ ላይ “የአሸባሪነት” ታርጋ አስለጥፎበታል፡፡

Monday 23 September 2013

የኦሮሞ ወጣቶች




Ka’i, Qeeroo
የኦሮሞ ወጣቶች ንቅናቄ መግለጫ
የኦሮሞ ወጣቶች ንቅናቄ ለነፃነትና ለዲሞክራሲ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ፖለቲካ አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ በቱኒዚያ፡ በግብፅና  በሌሎችም በመካከለኛዉ ምስራቅ እና በሰሜን አፍሪቃ በመካሄድ ላይ ያሉት የህዝብ  አመጾች በተመሳሳይ ጭቆና ሥር ላሉ እንደ ኢትዮጵያ ያሉ የአለም ክፍሎች  አርዓያነት ያለው መልዕክት መስተላለፉን ገልጿል።
በኢትዮጵያ ለሚታየዉ የለዉጥ ፍላጎት መነሳሳት እነዚሁ የሕዝብ አመጾች ምክንያት  እንደሆኑና ወቅቱ የአምባገነንና የፈላጭ ቆራጭ የፖለቲካ ስርኣቶች ተወግደዉ  ዲሞክራሲያዊና የህዝቦች ሉኣላዊነት  የሚሰፍንበት እንደሆነ አመልክቷል።
በኢትዮጵያ ለሚቀጣጠለዉ አመፅ መሰረታዊ ምክንያት የሚሆኑትና የሚያጎለብቱት  የሚያደርጉት በአገሪቱ ዉስጥ የሚታዩት ሁኔታዎች እንደሆኑ በመግለጫዉ  ተጠቅሷል። በመሆኑም ይላል መግለጫዉ “እኛ የኦሮሞና የሌሎችም ጭቁን ሕዝቦች ተማሪዎች የህዝባዊ አመፁን ለመለኮስ የመጀመሪያዎቹ ለመሆን ቁርጠኝነት እንዳለን  ለአለምና ለኢትዮጵያ ህዝብ እናረጋግጣለን። በባርነት ከመኖር በነፃነት መሞትን  መርጠናል የሚለዉ መግለጫ “‘ ስቃይና ባርነቱ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ አሁኑኑ  እንዲወገድና ነፃነትና ዲሞክራሲ እንዲሰፍን ያቀጣጠልነዉን ችቦ ቀሪዉ የኢትዮጵያ  ህዝብ ይዞ እንደሚከተለን አምነት አለን”‘ የሚለዉ መግለጫ ሰባት ንጥቦችን አስቀምጧል።
1. የህወሃት/ኢህአዴግ አገዛዝ በስታሊናዊ ድርጅታዊ መዋቅሩም ሆነ  በሚያራምዳቸዉ ማህበራዊና ፖለቲካዊ አጀንዳዎች  በጠባብ ጎሰኝነት ላይ  የተመሰረተ፡ በአገሪቱ ዘረጋሁ የሚለዉ የፌዴራል መዋቅር ለከፋፍለህ ግዛዉ  አላማዉ ካልሆነ በስተቀር ምንም ትርጉም የሌለዉ፡ የኦሮሞ፡ የኦጋዴን፡ የሲዳማ  እና የሌሎችንም የደቡብ ብሄር ብሄረሰቦች በዋና ጠላትነት ያነጣጠረ  መሆኑን  በመግለፅ… ላለፉት 20′ አመታት በኦሮሞ፡ በኦጋዴንና በሌሎችም ጭቆና  ላለፉት 20′ አመታት በኦሮሞ፡ በኦጋዴንና በሌሎችም ጭቆና  በበዘባቸዉ አካባቢዎች የሚገኙ ህዝቦች የሚያነሱትን ጥያቄ በሃይልና በህገ ወጥ  መንገድ ለማፈን የሚደረገዉ ወታደራዊ ዘመቻ በአስቸኳይ እንዲቆም

Sunday 22 September 2013

ሌ/ጀነራል ገዛኢ አበራ ቤተሰቦቻቸውን ሰብሰበው ስዊድን ገቡ


(ዘ-ሐበሻ) የጦር ሃይሎች የሎጂስቲክስ ዋና ሐላፊ የነበሩት ሌ/ጀነራል ገዛኢ አበራ ቤተሰቦቻቸውን ሰብስበው ስዊድን መግባታቸውን አብርሃ ደስታ ከመቀሌ ባስተላለፈው መረጃ አመለከተ። አብርሃም ገዛኢ ከሃገር የወጡት በጡረታ ለተገለሉ በኋላ ነው  በማላት  ”የህወሓት ሃላፊዎችማ የያዙትን ይዘው ከሀገር እየወጡ ነው። የተቸገሩ ታችኞቹ ካድሬዎች ናቸው። እንደ አለቆቻቸው ወደ ዉጭ በመኮብለል የግል ደህንነታቸው መጠበቅ አይችሉም።” ሲል ትችቱን አስፍሯል።
ጄነራል ገዛኢ አበራ በሱዳን አቢ ግዛት ሰፍሮ የነበረውን የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ሃይል የመሩ ናቸው።
ከአንድ ዓመት በፊት የግንቦት 7 የኢትዮጵያ የጥናት ቡድን ባሰራጨው ምስጢራዊ መረጃ ወያኔ የአገዛዝ እድሜውን ለማራዘም የትግራይ ተወላጆች የሆኑትን የጦር አለቆች ከፍተኛ የሆነ ሃብት እንዲያካብቱና ዘረፋ እንዲፈጽሙ ሁኔታዎችን ማመቻቸት ለተለያዩት የጦር መኮንኖች ሟቹ ጠ/ሚ/ር በ1989 ለአ/አበባ አስተዳደርና ለመከላከያ ሚ/ር መ/ቤት ለ25 የወያኔ የጦር መኮንኖች፣ ለእያንዳንዳቸው በሽልማት በአዲስ አበባ ውስጥ 500 ካሬ ሜትር 1ኛ ደረጃ መሬት እንዲሰጣቸው ትእዛዝ በሰጡት መሰረት ይህን መሬት የተቀበሉት ሌ/ጄነራል ገዛኢ አበራ በወር 170 ሺህ ብር የሚከራይ ቤት ቦሌ አካባቢ ሠርተው እንደሚያከራዩ ተጋልጦ ነበር።

የአባይ ቡድን በሁለት ተከፈለ!


------------------------------------

ህወሓት በአባይ ወልዱና ደብረፅዮን ቡድኖች በሁለት መከፈሉ ይታወቃል። ባለፈው የህወሓት የማእከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ የአባይና የደብረፅዮን ጠብ በጣም በመክረሩ የተነሳ ሽጉጥ መማዘዛቸው ተሰምቷል። ሃይለማርያም ደሳለኝና በረከት ስምዖን ለማስታረቅ የሞከሩ ሲሆን ዉጤቱ አልታወቅም።

ይህ በንዲህ እንዳለ የአባይ ቡድንም ሰሞኑ በሁለት ተከፍሏል፤ የአባይ ወልዱና የበየነ መክሩ። ከህወሓት ስብሰባ በኋላ የስልጣን ሽግሽግ ለማድረግ የተሞከረ ቢሆንም በየነ መክሩና ኪሮስ ቢተው ከስልጣናቸው ለመውረድ (ሓላፊነት ለመቀየር) ፍቃደኛ ባለመሆናቸው ከአባይ ወልዱ ጋር ከፍተኛ አምባጓሮ ተፈጥሯል።

ኪሮስ ቢተው የግብርና ቢሮ ሓላፊና የኢንተርፕራይዞች የቦርድ ሰብሳቢ ነበር። አባይ ወደ ሌላ ቢሮ ሊቀይሮው አስቦ ፍቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል። የኢንተርፕራይዞች (ብዙ በጀት የሚመደብበት) ስልጣን ግን ቀምቶ ለአለም ገብረዋህድ ሰጥቶታል። ግብርና ቢሮም ለወደ አዳል ታስቦ ነበር። ግን ጠብ ስለተነሳ አልተሳካም። በየነ መክሩም የንግድና ኢንዱስትሪ (የከተማ ልማት ጨምሮ) ስልጣን በእጁ ሲሆን አባይ ቢሮው ለሌላ ሊሰጠው ፈልጎ ፍቃደኛ ባለመሆኑ ግን እስካሁን ውዝግብ ላይ ናቸው። በየነ መክሩ ወደ ሀገሩ (እስራኤል) የመሄድ ሓሳብ ይዟል።

የአባይ ቡድን በሁለት መከፈሉ (አባይና በየነ የሚመሩት) ማሳያ በትግራይ ክልል የዉሃ ሃብት ቢሮ አመራር አባላት የሁለቱ ቡድኖች ደጋፊዎች ተጣልተው እንደተደባደቡና አከባቢው እስካሁን በፌደራል ፖሊስ እየተጠበቀ መሆኑ ተረጋግጧል።

ስርዓት ሲበሰብስ እንዲህ ነው። ለማንኛውም ቸር ያሰማን።

It is so!!!

ክ አብረህ ደስታ

Saturday 21 September 2013

የአቶ ቡልቻ መጽሐፍ ለንባብ በቃ

የአቶ ቡልቻ መጽሐፍ  ለንባብ በቃ
“ህይወቴ እና ለኦሮሞ እና ለሌሎችም የኢትዮጵያ ህዝቦች ያለኝ ራዕይ” በሚል ርዕስ በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀው የአቶ ቡልቻ ደመቅሳ መጽሐፍ በአሜሪካ ታትሞ በውጭ አገራት ለገበያ ቀረበ፡፡ መፅሃፉ አቶ ቡልቻ ከተወለዱባት የቦጂ በርመጂ ወረዳ ጀምሮ ከኦፌዴን ሊቀመንበርነት እስከለቀቁበት ጊዜ ድረስ ያሳለፉትን የትምህርት፣ የስራ እና የፖለቲካ ህይወት ይዳስሳል፡፡ ዘመናዊ ትምህርት ለመማር ያደረጓቸውን እልህ አስጨራሽ ሙከራዎች፣ ከአሜሪካን በኢኮኖሚክስ ተመርቀው ከመጡ በኋላ በገንዘብ ሚኒስቴር ውስጥ በምክትል ሚኒስትር ማዕረግ ባገለገሉባቸው አመታት ያጋጠሟቸውን ውጣ ውረዶች፣ በአለም ባንክ የኢትዮጵያ ተወካይ በመሆን እንዲሁም በዩኤንዲፒ ስለሠሯቸው ስራዎች በመጽሐፋቸው ተርከዋል፡፡

የኦሮሞ ህዝብን ጥያቄ አንስተው በፖለቲካው መስክ ስላደረጉት ተሳትፎ የፃፉት አቶ ቡልቻ፤ አዋሽ ባንክን ለመመስረት ያደረጉትን አስተዋጽኦና በባንኩ ውስጥ የተፈጠረውን አለመግባባትም በስፋት ዳስሰዋል፡፡ መጽሐፉ 180 ገፆች ያሉትና በ20 ምዕራፎች የተከፋፈለ ሲሆን በኦሮሚኛ እና በአማርኛ ቋንቋዎች ተተርጉሞ ለአገር ውስጥ ገበያ እንደሚቀርብ አቶ ቡልቻ ደመቅሳ ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡
http://www.addisadmassnews.com

ለፕሬዚዳንት ግርማ በወር በ530 ሺሕ ብር ቤት ለመከራየት የተፈረመው ውል ፈረሰ


የፕሬዚዳንትነት ቆይታቸውን በማጠናቀቅ ላለፉት 12 ዓመታት የቆዩበትን ብሔራዊ ቤተ መንግሥት ለአዲሱ ፕሬዚዳንት እንደሚያስረክቡ ለሚጠበቁት ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ መኖሪያ እንዲሆን በወር 530 ሺሕ ብር የሚከፈልበት ቤት ለመከራየት የተገባው ውል ተሰረዘ፡፡
ምንጮች እንደገለጹት፣ ፕሬዚዳንት ግርማ በቅርቡ ከቤተ መንግሥት ሲለቁ ከነቤተሰቦቻቸው እስከ ሕይወት ፍፃሜያቸው ይኖሩበታል ተብሎ የተመረጠውና በወር 530 ሺሕ ብር ለመክፈል ከቤቱ ባለቤት ጋር የተደረገው ስምምነት፣ የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ጽሕፈት ቤት ቀርቦ ውል ታስሮበት ነበር፡፡ ሆኖም የኪራይ ስምምነቱ ውል ከተፈረመ ከሁለት ሳምንታት በኋላ የፕሬዚዳንቱ ጽሕፈት ቤት ውሉ እንዲቋረጥ መወሰኑን አስታውቋል፡፡ 
አዲስ አበባ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 ውስጥ የሚገኘውን ለፕሬዚዳንት ግርማ መኖሪያ የተመረጠውን ቤት ለመከራየት ከአከራዩ ጋር የኪራይ ውል ስምምነት ያደረገው  የፕሬዚዳንቱ ጽሕፈት ቤት ነበር፡፡ ቀድሞም ቢሆን ስምምነቱ የተጋነነና ለG+1 መኖሪያ ቤት ይህን ያህል ዋጋ ይከፈላል የሚል ሙግት ቀርቦ እንደነበር ምንጮች ገልጸዋል፡፡ ስምምነቱ በይፋ ከተፈረመ በኋላ ግን የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ጭምር ኪራይ ተገቢ አይደለም በማለት ውሳኔ በማስተላለፋቸው፣ የፕሬዚዳንቱ ጽሕፈት ቤት በውሉ ውስጥ የተካተቱትንና ውሉን ለማፍረስ ያስችሉኛል ያላቸውን አንቀጾች በመጥቀስ እንዲሰረዝ አድርጓል፡፡ ይህንንም የመኖሪያ ቤቱን ለማከራየት ውል ለገቡት ባለንብረት በደብዳቤ ማስታወቁንም ምንጮች ገልጸዋል፡፡ የኪራይ ስምምነቱን የመዘገበው የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ጽሕፈት ቤትም ውሉ መሰረዙን እንዲያውቅ የፕሬዚዳንቱ ጽሕፈት ቤት ደብዳቤ ጽፏል ተብሏል፡፡ 

Friday 20 September 2013

Women's group submits human rights report on Ethiopia to UN


EWHRA
September 20, 2013

Grassroots organization details human rights violations committed by the Ethiopian government and outlines recommendations to bring Ethiopia into compliance with international law.

New York -- Ethiopian Women’s Human Rights Alliance (EWHRA) released a report on Thursday that was submitted to the Universal Periodic Review (UPR), a United Nations (UN) mechanism aimed at reviewing the human rights record of UN member countries. EWHRA’s Report details the egregious violation of human rights committed by the Ethiopian government in contravention of its obligations under numerous international human rights treaties.
While the Ethiopian government continues to violate international standards with regard to myriad fundamental human rights, in its report, EWHRA concentrates primarily on the following issues: freedom of expression, freedom of association and political rights, freedom of religion, persecution of ethnic groups and forced displacement of indigenous people from ancestral lands and freedom from arbitrary arrests and detentions.
“EWHRA is pleased that we were asked to participate in this extremely important review of the Ethiopian government’s abhorrent record on human rights. EWHRA’s goal is ensuring that the voices of the eighty million women, children and men suffering under the current regime are heard and that those responsible for violating internationally recognized rights are held accountable,” said a representative of the grassroots organization.

አሳዛኙ የወገናችን ኅልፈት

"ህይወት እንደዋዛ"

the pic


ዲፕሎማቱ እጅ ላይ ያረፈችው ኢትዮጵያዊት ወጣት ሬሳ ትላንት ከሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ግቢ ወዳልታወቀ ስፍራ ተወሰደ ።
ቀን መስከረም 8: 2006 ለ5ኛ ግዜ በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ግዜያዊ መጠለያ ኮኔትነር ውስጥ፡ የአንዲት ኢትዮጵያዊት አስዛኝ፡ ህልፈተ ህይወት የአካባቢውን ማህበረሰብ እምባ ሲያራጭ፡ ደረት ሲያዳቃ መዋሉን የአይን ምስክሮች ገለጹ። ወጣቷ በቤት ሰራተኝነት ኮንትራት የመጣች የክርስትና እምነት ተከታይ መሆኗን የሚናገሩት እነዚህ የአይን እማኞች የወጣቷ ሬሳ እስካሁን በውል ወዳልታወቀ ስፍራ መወሰዱን አረጋግጠዋል።
የእህቶቻችን ሞት ከሚፈበረክበት በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ማህበር የስደተኞች ጊዜ ያዊ መጠለያ ኮንቴነር፡ ያለምንም ህክምና እና በቂ መሰረታዊ ፍጆታ በለሌለበት ሁኔታ እንደ ወንጀለኛ የኮንቴነር የብረት በር ተከርችሞባቸው ከሚገኙ እህቶቻችን መሃከል አንድ ወር ባልሞላ ግዜ ውስጥ በተከታታይ የሁለት ኢትዮጵያውያን ህልፈተ ህይወት መሰማቱ የአካባቢውን ማህበረሰብ አስደንግጦል።
በተለይ ትላንት ማለዳ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከጠዋቱ 3 አካባቢ አስከሬንዋ ጊዜያዊ መጠለያ ኮንቴነር ውስጥ ሞታ የተገኘችው ኢትዮጵያዊት ወጣት ህመሙ አገርሽቶባት ስታቃስት «ጣዕረሞት ስታሰማ»፡ እንደ ነበር የሚናገሩ ወገኖች ዲፕሎማቱ ትብብር እንዲያደርጉላት ስልክ ቢደወልላቸውም በወቅቱ ፈቃደኛ ባለመሆናቸው የወጣቷ ህይወት በሚያሳዝን ሁኔታ ማለፉን ይገልጻሉ።

Thursday 19 September 2013

ከፍተኛ መሬት መንቀጥቀጥ በኤርትራ ተከሰተ በሱዳን እንደተሰማም ተገለጸ


massawa


ረቡዕ መስከረም 8፤2006ዓም ልክ በ6፡08 ሰዓት ላይ በኤርትራ የመሬት መንቀጥቀጥ መድረሱን CMI የተሰኘው የጣሊያን ዜና ወኪል አስታውቋል፡፡
በተለያዩ የዓለም ተቋማት የተገኘው መረጃ እንደሚያብራራው የመሬት መንቀጥቀጡ የተነሳው ከምጽዋ ጥቂት ኪሎሜትሮች ወጣ በማለት እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡ መጠኑ 5.0 ነው የተባለለት የመሬት መንቀጥቀጥ 18ሺህ ሕዝብ በሚኖርባት ምጽዋም ሆነ ባካባቢው ያደረሰውን ጉዳት ለማወቅ በቂ መረጃ እንደሌለ የዜና ወኪሉ ጠቁሟል፡፡
የመሬት መንቀጥቀጡ በሱዳን መሰማቱንም የሱዳን ትሪቢዩን ዘግቧል፡፡ በተመሳሳይ ሰዓት አካባቢ መድረሱ የጠቆመው ዜና የሱዳን ከርሰ ምድር ጥናት ማዕከል 5.9 መጠን ያለው ስለመሆኑ የሰጠውን ማስረጃ በማከል አቅርቧል፡፡
የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስቴር የመሬት መንቀጥቀጥ መድረሱንና ሰዓቱ ከመግለጽ በስተቀር ስለደረሰው ጉዳት የሰጠው መግለጫ የለም፡፡
ከባህር ውስጥ የሚነሳ የመሬት መንቀጥቀጥ የሱናሚ ዓይነት ተጽዕኖ ያለውና የሚያደርሰው ጥፋት ከመንቀጥቀጡ ጋር አብሮ የሚያስነሳው ማዕበልና ጎርፍ እንደሆነ ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡ (ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ)

ተቃዋሚዎች በመስቀል አደባባይ ሰላማዊ ሰልፍ እንዳያደርጉ ተከለከሉ

መስከረም ፱(ዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- መስከረም 12 እና መስከረም 19 ሰማያዊ እና አንድነት ፓርቲዎች በተከታታይ የጠሩዋቸው ሰልፎች በመስቀል አደባባይ እንደማይካሄዱ የአዲስ አበባ መስተዳድር ህዝባዊ ስብሰባ ማስታወቂያ ክፍል አስታውቋል።

ጽህፈት ቤቱ ይህን ያስታወቀው ከሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ጋር ውይይት ካደረገ በሁዋላ ነው።
ይህንን ውሳኔ ተከትሎ ፓርቲው ባወጣው መግለጫ ” ህዝባዊ አገልግሎት የሚሰጥ ቦታ ለዜጎች ሁሉ መብት የሆነውን ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብት በህግ ለተቋቋመና ህዝባዊ ሀላፊነትን ለወሰደ የፖለቲካ ፓርቲ መከልከልና እስከዛሬም ድረስ ከገዢ ፓርቲ ጀምሮ ሌሎች አካላት በመስቀል አደባባይ በተደጋጋሚ ሰልፍ ያደረጉበት መሆኑ እየታወቀ እንደዚህ አይነት ሚዛናዊነት የጎደለው አሰራር መቀበልና በቸልታ ማለፍ ፓርቲያችን ከተመሰረተበት አላማ ጋር የሚጋጭ፣ ከሞራል ፣ከህግና ከፖለቲካ አንጻርም ተቀባይነት የሌለው” አሰራር ነው ብሎአል።
ሰማያዊ ፓርቲ የፊታችን እሁድ በመስቀል አደባባይ የሚያደርገውን የተቃውሞ ሰልፍ እንደማይለውጥ አስታውቋል። ፓርቲው ነሐሴ 26 የጠራው ሰልፍ በጸጥታ ሀይሎች እንዲደናቀፍ መደረጉ ይታወሳል።
አንድነት ፓርቲም በተመሳሳይ መልኩ መስከረም 19 ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ እንደማይችል  እንደተገለጸለት የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ ዳንኤል ተፈራ ተናግረዋል

አና ጎመሽ - ርዕዮትና እስክንድር “የኅሊና እሥረኞች ናቸው” አሉ

ለያዝነው የአውሮፓ 2013 ዓ.ም የአውሮፓ ፓርላማ የሳኻሮቭ ሽልማት ሁለት ኢትዮጵያዊያንን ጨምሮ ሰባት ዕጩዎች ቀርበዋል፡፡


አና ጎመሽ - የአውሮፓ ፓርላማ አባል
አና ጎመሽ - የአውሮፓ ፓርላማ አባል
ለያዝነው የአውሮፓ 2013 ዓ.ም የአውሮፓ ፓርላማ የሳኻሮቭ ሽልማት ሁለት ኢትዮጵያዊያንን ጨምሮ ሰባት ዕጩዎች ቀርበዋል፡፡

Wednesday 18 September 2013

ኢትዮጵያ፥ የሥልክና የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ሮሮ

«የደወሉት ቁጥር ከአግልግሎት መስጪያ ክልል ዉጪ ነዉ።» ትላለኝ አንዷ፥ «የደወሉላቸዉን ደንበኛ አሁን ማግኘት አይችሉም-» ደንበኛዉ ከጎንዎ ተቀምጦ ሊሆንም ይችላል። ብቻ -The Net work is Busy Now----እያለች ትቀጥላለች፥ ሌለኛዋ።ያንኑ ቁጥር ደግመዉ ይሞክሩ----መጀመሪያ ከሰሙት የተለየ መልዕክት ይሰማሉ

Nokia mobile phones in Helsinki, Finland April 16, 2009. Nokia releases first-quarter figures on Thursday. LEHTIKUVA / Heikki Saukkomaa +++(c) dpa - Report+++
«ካገልግሎት መስጪያ---ዉጪ»
እዚያዉ ኢትዮጵያ፥ ከፈለጉ አሜሪካ፥ ወይም አዉሮጳ ቻይናም ይሁኑ ብቻ ወደ ኢትዮጵያ ሥልክ ይደዉሉ።ብዙ ጊዜ ከስልኩ የወዲያኛዉ መስመር የሚሰሙት ለስለስ፥ ለዘብ፥ ረጋ ያለ ድምፅ ዘና ያደርግዎት-ይሆን ይሆናል።መልዕክቱ ግን በምንም መንገድ ሊያስደስትዎ አይችልም።«የደወሉት ቁጥር ከአግልግሎት መስጪያ ክልል ዉጪ ነዉ።» ትላለኝ አንዷ፥ «የደወሉላቸዉን ደንበኛ አሁን ማግኘት አይችሉም-» ደንበኛዉ ከጎንዎ ተቀምጦ ሊሆንም ይችላል። ብቻ -The Network Is Busy Now----እያለች ትቀጥላለች፥ ሌለኛዋ።ያንኑ ቁጥር ደግመዉ ይሞክሩ----መጀመሪያ ከሰሙት የተለየ መልዕክት ይሰማሉ።የኢትዮጵያ መንግሥት ብቻዉን የሚቆጣጠረዉ ኢትዮ-ቴሌኮም የኢንተርኔት አገልግሎቱም (አንዳዶች የሌለ ነገር አገልግሎት አይባልም ይላሉ)---የባሰ ነዉ።

የቤተመንግስት ደህንነት ሃላፊ ተነሱ (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

 

የነአዜብ ቡድን እየተመታ ነው!!
 
የቤተ-መንግስት የደህንነት ጥበቃ ዋና ሃላፊ ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩት የሕወሐት አባል አቶ ጌታቸው ተፈሪ ከስልጣናቸው መነሳታቸውን ምንጮች አስታወቁ። አቶ ጌታቸው ቀደም ሲል በክልል 14 ፖሊስ ኮሚሽን የደሕንነት ልዩ ተወርዋሪ ሃይል ሃላፊ ተደርገው ሲያገለግሉ መቆየታቸውን የጠቆሙት ምንጮች፣ ከዚያም ወደ ቤተ መንግስት ተዛውረው መመደባቸውንና በተጨማሪ የአገር ውስጥ ደህንነት ምክትል ሃላፊ በመሆን ከአቶ ወ/ስላሴ ወ/ሚካኤል ጋር ሲሰሩ መቆየታቸውን አስረድተዋል። የአቶ መለስና ወ/ሮ አዜብ የቅርብ ሰው የሆኑት አቶ ጌታቸው ተፈሪ በነበራቸው ታማኝነት የቤተመንግስት የደህንነት ሃላፊ ተደርገው በአቶ መለስ ተመርጠው እንደተሾሙ ያስታወሱት ምንጮች፣ በማያያዝም እስከ 1994ዓ.ም የቤተመንግስት የደህንነት ጥበቃ በሃላፊነት ሲመሩ የቆዩት አቶ ዘርኡ መለስ በወቅቱ ከአቶ መለስ ጋር በፈጠሩት የፖለቲካ ልይነት ምክንያት ካዛንቺስ አካባቢ በሚገኘው የቀድሞ “ኮከብ ሬስቶራንት” የአሁኑ “ሚልክ ሃውስ” መኖሪያ ሕንፃ አንደኛ ፎቅ ቤታቸው ውስጥ አንገታቸው በስለት ታርዶና በድናቸው ተበላሽቶ መገኘቱን አመልክተዋል። ይህን አሰቃቂ ግድያ ያከናወነው አሁን በእስር ቤት የሚገኘው የቀድሞ አገር ውስጥ ደህንነት ሃላፊና የአቶ መለስ ቀኝ እጅ ወ/ስላሴ ወ/ሚካኤል መሆኑን ምንጮቹ አጋልጠዋል።
የነ አዜብ ቡድን እየተመታ ነው!
የነ አዜብ ቡድን እየተመታ ነው!
አቶ ጌታቸው ተፈሪ ከስልጣን እንዲነሱ የተደረገው በደህንነት ዋና ሹም አቶ ጌታቸው አሰፋ ትእዛዝ መሆኑን ያመለከቱት ምንጮች፣ በአሁኑ ወቅት በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ እንደማይታወቅ ጠቁመዋል። አቶ ጌታቸው ተፈሪ — የወ/ስላሴ መታሰር ቅር ሳያሰኛቸው እንዳልቀረና በተጨማሪም የነአዜብ ቡድን ደጋፊ መሆናቸውን ምንጮቹ አመልክተዋል።

Remembering Oromo Prisoner of Consciousness: Taye Danda’a in Prison for being only Oromo

September 17, 2013
My name is Taye Danda'aa , I am in jail. I am criminal for being Born as an Oromo. I was sentenced 10 years in prison. I was graduated as a lawyer and offered to be a lecturer in A.A university
My name is Taye Danda’aa , I am in jail. I am criminal for being Born as an Oromo. I was sentenced to 10 years in prison. I was graduated as a lawyer and offered to be a lecturer  at AAU.
Taye Danda’a Araddo was an outstanding student of Law at Addis Ababa University (AAU) and a role model for many students. He had received countless awards from the district-level to Caffee Oromiyyaa for his academic successes. He had been in jail from 2003-2006 due to his political views. Without giving up, after his release, he went back to school and continued his education till his arrest three days before his graduation in 2009. He has been a star student, and he had been hired by AAU as a professor before his latest arrest by Ethiopian government authorities. Taye is in prison since 2009.

Background

HRLHA Press Release No. 18, Aug 2009
According to documents obtained by the Human Rights League of the Horn of Africa (HRLHA) from its informants in Addis Ababa, another wave of arrests and imprisonments targeting prominent Oromo intellectuals, students and businessmen is going on in different parts of the State of Oromia, including its capital Addis Ababa. The arbitrary arrests and detentions, which are mainly being carried out by security agents deployed in civilian clothing, started following an updated allegation that the local residents harbor and/or support the opposition armed group – the Oromo Liberation Front (OLF).
With this most recent wave of arrests, dozens of Oromo nationals have already been taken into custody. This includes:

Tuesday 17 September 2013

የርዕዮት አለሙ የስር ቤት አያያዝ

የወጣት ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ የእስር ቤት አያያዝ እየተባባሰ እንጂ እየተሻሻለ አለመሆኑ ተሰማ።

CPJ logo, COMMITTEE TO PROTECT JOURNALISTS, graphic element on white 2008/11/26
Logo CPJ
ወላጅ አባቷና ጠበቃዋ እንደሚሉት የጠያቂዎቿ ቁጥር ቀንሷል፣ የእስር ቤት አልጋዋንም ለሌላ እስረኛ እንድትለቅ ተገዳለች። በሌላ በኩል ዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ ሴቶች ድርጅት እና ሌሎች ዓለም አቀፍ ተቋማትም ጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ ያለአንዳንች ቅድመ ሁኔታ እንድትፈታ እየጠየቁ ነው። «ባልፈጸመችው ወንጀል ይልቁንም በመብት ተሙዋጋችነትዋ በእስር ቤት ያውም ኢሰብኣዊ በሆነ አያያዝ እየማቀቀች የምትገነው ወጣት ጋዜጠና ርዕዮት አለሙ» ይላል ዓለም ዓቀፉ የኢትዮጵያ ሴቶች ድርጅት በምህፃሩ IEWO ባለፈው ዓርብ ባወጣው መግለጫ ለበርካታ ኢትዮጵያት ሴቶችም መልካም አርዓያነት መጠቀስ ከጀመረች ከራርማለች።
ከዚሁ የተነሳ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ እና ዓለም ዓቀፍ የመብት ተሟጋቾች ሁሉ ይህንኑ በመቃወም ርዕዮት ዓለሙን ጨምሮ ሌሎችም በግፍ ታስረው በእስር ቤት እየተሰቃዩ ናቸው ያላቸው እስረኖች ይፈቱ ዘንድ እንዲተባበሩ ዓለም ዓቀፍ ጥሪ ኣቅርበዋል። ርዕዮት አለሙ በዘመናችን ወደር በሌለው ጀግንነት ከሚወደሱት ጥቂት ኢትዮጵያን መካከል ትጠቀሳለች ያለው ድርጅቱ ለመፃፍ ነፃነቱዋ እና በኣጠቃላይ በመብት ተሟዋጋችነቱዋ በምትከፍለው መስዋትነት ሁሉ ድጋፋችን እንደማይለያት እናረጋግጣለን ብለዋል።

ሮቤል ፍሊጶስ ለተመሰረተበት ክስ ጥፋተኛ አይደለሁም አለ