Saturday 24 August 2013

ንብ ባንክ እና ንብ ኢንሹራንስ ባለ 35 ፎቅ ህንፃ ሊያስገነቡ ነው

Written by  መንግሥቱ አበበ


ንብ  ባንክ እና ንብ ኢንሹራንስ ባለ 35 ፎቅ ህንፃ ሊያስገነቡ ነው
ንብ ኢንተርናሽል ባንክ እና ንብ ኢንሹራንስ ኩባንያ ባለ 35 ፎቅ ህንፃ መሠረት ለማስገባት ከቻይናው “ሬይል ዌይ ነምበር ስሪ” ኩባንያ ጋር ተፈራረሙ፡፡
የሁለቱ እህትማማቾች ድርጅት ዋና መ/ቤት ህንፃ የሚገነባው ከብሄራዊ ቴያትር ጀርባ ነው፡፡
በአሰሪ ድርጅቶቹ በኩል ስምምነቱን የፈረሙት የንብ ኢንተርናሽናል ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ ክብሩ ፎንጃ እና የንብ ኢንሹራንስ ኩባንያ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ኃ/ማርያም አሰፋ ሲሆኑ፤ በተቋራጩ በኩል በኢትዮጵያ የድርጅቱ ተወካይ ሚ/ር ዛሆ ሳንባሆ ናቸው፡፡
የቻይናው “ሬይል ዌይ ነምበር ስሪ” ኩባንያ የዋና መ/ቤቱን ሕንፃ መሠረት አራት ፎቆች የሚያወጣ ሲሆን የሕንፃውን ቀሪ ፎቆች ሌላ ኮንትራክተር እንደሚሠራ ታውቋል፡፡ የሕንፃው ግንባታ በቅርቡ እንደሚጀመር የተገለፀ ሲሆን፣ ለባንኩና ለኢንሹራንስ ሠራተኞች ለቢሮና ለባንክ አገልግሎት የሚውሉ ክፍሎች እንደሚኖሩት ታውቋል፡፡

ሕንፃው ዘመናዊ የደህንነት ጥበቃ መሳሪያዎች የሚገጠሙለት ሲሆን ለደንበኞች ምቹና ቀልጣፋ አገልገሎት ለመስጠት ከወለል በታች ባለ 4 ፎቅ የመኪና ማቆሚያ እንደሚኖረው ተገልጿል፡፡
ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ አ.ማ ከተመሠረተ 14 ዓመት ሲሆነው ከ300ሺህ በላይ የአክሲዮን አባላትና ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ የተከፈለ ካፒታል እንዳለው ታውቋል፡

addis admas

No comments:

Post a Comment