Saturday 27 July 2013

ሰበር ዜና፣ የአንድነት ፓርቲ አመራሮች ቤት በፖሊሶች እየተበረበረ ነው

July 27, 2013

ብርበራው ቀኑን ሙሉ እንደሚደረግ ታውቋል

በደቡብ ወሎ ዞን በሀይቅ ከተማ የሚገኙ የአንድነት ፓርቲ አመራሮችና አባላት ቤት ላይ ዛሬ ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ ብርበራ እንደተጀመረ የዞኑ የአንድነት ፓርቲ አመራሮች ለፍኖተ ነፃነት አስታወቁ፡፡
የአንድነት ፓርቲ የወረባቡ ወረዳ ሰብሳቢ አቶ እድሪስ ሰኢድ ለፍኖተ ነፃነት እንዳስታወቁት ዛሬ ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ “የጦር መሳሪያ ሰውራችኋል” በሚል ፖሊሶችና ሚኒሻዎች በሀይቅ ከተማ ባሉ ከ16 በላይ በሚሆኑ የአንድነት ፓርቲ አመራሮችና አባላት መኖሪያ ቤት ውስጥ ብርበራ አካሂደዋል፡፡ ብርበራው ከተካሄደባቸው አመራሮች መሀከል አንዱ የሆኑት የወረዳው የአንድነት ፓርቲ የፋይናንስ ኃላፊ አቶ አራጌ ሑሴን ለሪፖርተራችን እንደገለፁት 5 ፖሊሶችና 1 ሚሊሻ ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምረው መኖሪያ ቤታቸውን ፈትሸዋል፡፡ አቶ አራጌ ሁሴን አክለውም “እኔ ሰላማዊ ሰው ነኝ ምንም አታገኙም አልኳቸው፤እንዳልኩትም 2 ሰዓት የፈጀ ብርበራ አድርገውም አንዳች ሳያገኙ ወጥተዋል” በማለት ገልፀዋል፡፡

በኦሮሚያ 10 ተጠርጣሪ ሙሰኞች በቁጥጥር ሥር ዋሉ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ ተመዝብሯል

owwce


  • ተጠርጣሪዎቹ ሽፈራው ጃርሶ የሚመሩት ቦርድ ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች ናቸው
ከሙስና ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ አሥር የኦሮሚያ ክልል ውኃ ሥራዎችና ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ባለፈው ሰኞ በቁጥጥር ሥር ዋሉ፡፡
ኮሚሽኑ በቁጥጥር ሥር ካዋላቸው ከእነዚህ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተጨማሪ፣  ሌሎች 15 የሥራ ኃላፊዎችን በቁጥጥር ሥር ለማዋል የፍርድ ቤት ማዘዣ አውጥቶ ፍለጋ መጀመሩን ምንጮች ገልጸዋል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉት የኮንስትራክሽን ዕቃዎች ግዥና የመንግሥትን የፋይናንስ ሕግ ባልተከተለ መንገድ ኪራይ ፈጽመዋል በሚል ጥርጣሬ መሆኑን፣ የክልሉ ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን አስታውቋል፡፡ ኮሚሽኑ ለአንድ ዓመት ባካሄደው ጥናታዊ ምርመራ በዚህ የሙስና ወንጀል መንግሥትን በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ እንዳሳጣው ለጉዳዩ ቅርበት የኮሚሽኑ ምንጮች ገልጸዋል፡፡

Friday 26 July 2013

Dr. Wondimu Says Semhal Meles Deposits $5 Billion

 የመለስ ዜናዊ የመጀመሪያ ልጅ ሰመሃል መለስ ኒው ዮርክ ውስጥ በሚገኝ አንድ ባንክ ውስጥ 5 ቢሊዮን ዶላር በ2011 ኣስገብታለች። ይህን ያሉት እንግሊዝ አገር እሚገኙት ምሁር እና የመንግስት ተቃዋሚ የሆኑት ዶክተር ወንድሙ መኮንን ናቸው። ዶክተር ወንድሙ የቼኩን ኮፒ አያይዘው ለእንግሊዝ ፓርላማ ሃውስ ኦፍ ኮመንስ አቅርበዋል። ሙሉውን እዚህ ያገኛሉ

A cheque of $5 Billion lodged  by Semhal Meles in New York, Image Courtesy of Dr. Wondimu
July 26, 2013
Semehal Meles Zenawi, the daughter of the late Ethiopian Prime Minister Meles Zenawi, “has deposited $5 billion in one of the banks in New York”, said Dr. Wondimu Mekonnen, an academic and opposition figure, during a recent presentation at the House of Commons in the U.K.
Wondimu also showed and distributed to the members of the House who attended his presentation, what he called a “copy of the cheque of the money” she lodged.

Thursday 25 July 2013

Letter From Ethiopia’s Gulag

By ESKINDER NEGA

eskinderJuly 25, 2013, ADDIS ABABA, Ethiopia (The New York Times)  — I AM jailed, with around 200 other inmates, in a wide hall that looks like a warehouse. For all of us, there are only three toilets. Most of the inmates sleep on the floor, which has never been swept. About 1,000 prisoners share the small open space here at Kaliti Prison. One can guess our fate if a communicable disease breaks out.
I was arrested in September 2011 and detained for nine months before I was found guilty in June 2012 underEthiopia’s overly broad Anti-Terrorism Proclamation, which ostensibly covers the “planning, preparation, conspiracy, incitement and attempt” of terrorist acts. In reality, the law has been used as a pretext to detain journalists who criticize the government. Last July, I was sentenced to 18 years in prison.
I’ve never conspired to overthrow the government; all I did was report on the Arab Spring and suggest that something similar might happen in Ethiopia if the authoritarian regime didn’t reform. The state’s main evidence against me was a YouTube video of me, saying this at a public meeting. I also dared to question the government’s ludicrous claim that jailed journalists were terrorists.

Wednesday 24 July 2013

“ለዚህ (መንግሥት) ታላቅ ክብር አለኝ” ሃይሌ! ወደ ፓርላማ?


haile gebreselasse


የዛሬ 10 ወር የሻለቃ ሃይሌ ገ/ሥላሴ ወደ ፖለቲካ የመምጣት ሁኔታን አስመልክቶ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ሃተታ አቅርቦ ነበር፡፡ (እዚህ ላይ ይመልከቱት) ሰሞኑን አትሌቱ ወደ ፖለቲካው የመግባት ፍላጎቱንና “በምርጫ” ለመወዳደር መፈለጉ ብዙ እየተባለበት ይገኛል፡፡ ከዚህ አንጻር አሁን ላለው ሁኔታ ግንዛቤ ይሰጣል በማለት ከዚህ በፊት ያቀረብነውን ሃተታ በድጋሚ አትመነዋል፡፡

“ለኢትዮጵያ የጥምር መንግስት ያስፈልጋታል” በማለት በ1997 ምርጫ አጥብቆ ሲከራከር የነበረውና በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ ደረጃ ኢንቨስትመንት ውስጥ የገባው ሻለቃ ሃይሌ ገብረስላሴ በኢትዮጵያ ቀደም ሲል ከነበሩት መንግስታትና ትውልዶች ይልቅ አሁን ላለው ትውልድ ከበሬታ እንዳለው በመግለጽ አስተያየቱን ሰነዘረ። የክብር ሪኮርዶቹን በሙሉ ለቀነኒሳ ያስረከበው ሃይሌ በእጁ የሚገኘውን ብቸኛ ሃብቱን (የህዝብ ክብር) እያሟጠጠ መሆኑ እየተገለጸ ነው።
ሃይሌ ይህንን የተናገረው መስከረም 12 ቀን 2004 ዓ ም ከተለያዩ አስተያየት ሰጪዎች ጋር በመንግስት ቴሌቪዥን (ኢቲቪ) አስተያየት በሰጠበት ወቅት ነበር። የቀድሞውን ስርዓትና ትውልድ “ድንጋይ ዳቦ በነበረበት፣ ፍራፍሬ ከጫካ ያለምንም ድካም ከሚሰበሰብበት” ዘመን ጋር ያወዳደረው ሃይሌ፣ “የአሁኑ ትውልድ” በማለት ያሞካሸውን ስርዓት ከተፈጥሮ ጋር ጦርነት በማካሄድ ለውጥ ማስመዝገበ መቻላቸውን አስምሮበታል።

Oromo Political Prisoners Continue to Be Tortured by the Woyane Abyssinian Army

 

Human Rights Groups: Donor Countries Fuel Abuse in Ethiopia

by Selah Hennessy

July 23, 2013, LONDON (VOA News) — Two new reports published this month say sustainable development in Ethiopia is impossible without a specific focus on human rights. The reports say donor countries should bear responsibility for ensuring their aid money is not used to fuel abuse.
Ethiopia receives billions of dollars in international aid every year. It is money that is used to help improve basic services like access to health and education.
But human-rights campaigners say there also is widespread abuse that takes place in Africa’s second most populous country. And they say donors need to face up to what role their aid money might play in fueling that abuse.
Leslie Lefkow, the deputy director for Human Rights Watch’s Africa Division, said, “The Ethiopian government is resettling large numbers of pastoralists and semi-pastoralist communities in the name of better services. But often this resettlement process is accompanied by very serious abuses.”
Human rights groups say so-called “villagization” has been marred by violence, including rapes and beatings, and people are often forced to leave their homes against their will. They also say the new villages lack adequate food, farmland, healthcare and education facilities.

Tuesday 23 July 2013

ሰበር ዜና፣ አዲስ አበባ ከተማ በግድግዳ ጽሁፎች (ግራፊቲ) ተሸፍና አደረች

July 23, 2013

ድምፃችን ይሰማ
ሰኞ ሐምሌ 15/2005
እሁድ ምሽት ለሰኞ አጥቢያ በአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ ቦታዎች የሙስሊሙን ህብረተሰብ ጥያቄዎች በሚያንጸባርቁ ጥቅሶች ተጽፎባቸው አደሩ፡፡ በከተማዋ የተለያዩ መንገዶች፣ የመንገድ አካፋዮች እና አጥሮች ላይ መንግስት ሕገ መንግሰቱን እንዲያከብርና በእምነት ጣልቃ መግባቱን እንዲያቆም የሚጠይቁ ጽሁፎች በትላልቅ ቁመት ለህዝብ በሚታይ መልኩ ተጽፈው የተገኙ ሲሆን ይህ በተጻፈባቸው ቦታዎችም ሰዎች ሁኔታውን በትኩረትና በግርምት ሲመለከቱ እንደነበር ታውቋል፡፡Ethiopian Muslims protest, Addis Ababa1
በካዛንቺስ፣ በጦርሀይሎች በውንጌት አስኮ መንገድ እንዲሁም ገና በውል ባልታወቁ ቦታዎች ደምጻችን ይሰማ፣ ኮሚቴው ይፈታ፣ ሕገ መንግስቱ ይከበር፣ ጥያቄያችን ይመለስ፣ በእምነታችን ጣልቃ አትግቡብን የሚሉ ጽሁፎች ተጽፈው የታዩ ሲሆን በካባቢው የሚገኙ የወረዳ አስተዳደሮችም በተፈጠረው ነገር በመደናገጥ ጽሁፎቹን ለማጥፋት ጥረት እያደረጉ ይገኛል፡፡ የጎዳና እና የግድግዳ ጽሁፎች በአለም የታወቁ የመቃወሚያ ዘዴዎች በመሆናቸው ህብረተሰቡ መልእክቱን ለሚመለከተው አካል ለማድረስ የሚጠቀምባቸው ናቸው፡፡
ሙስሊሙ ህብረተሰብ ሕጋዊ የመብት ጥያቄዎቹን አግባብ ባለው መልኩ ለመንግስት ሲያቀርብ እንደነበር የሚታወቅ ሲሆን አሁንም በዚህ እርምጃው በመቀጠልና ወደ ሌላ ሂደትም በመሸጋገር መንግስት ለሚወስዳቸው ማንኛውም እርምጃዎች እጅ እንደማይሰጥ በማሳየት ላይ የሚገኝ መሆኑን ይህ የዛሬ ክስተት ምስክርነቱን ሰጥቷል፡፡ መንግስት የሙስሊሙን ጥያቄ ከመመለስ ይልቅ ሙስሊሙን በአክራነትና አሸባሪነት በመፈረጅ ላይ የሚገኝ ቢሆንም ሙስሊሙ ህብረተሰብ በተገኙት አጋጣሚዎች ሁሉ ድምጹን ለማሰማትና መንግስት ምላሹን እንዲሰጥ ለማድረግ ጥረቶች በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ በዚህ አይነቱ ስልትም ሆነ በሌሎች ሰላማዊ መንገዶችና የመታገያ ስልቶች የሙስሊሙን ህብረተሰብ ሕጋዊ ጥቄዎች ብቻ የሚያንጸባርቁና ከትግሉ መንፈስ ያልወጡ መልእክቶች ሊተላለፉበት እንደሚችሉ ይታሰባል፡፡

Monday 22 July 2013

በቂሊንጦ የሚገኙ እስረኞች በሞት አፋፍ ላይ እንገኛለን አሉ

ሐምሌ ፲፭(አስራ አንድ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በእነ አቶ ተሻለ በካሻ መዝገብ ተከሰው ከሁለት አመታት በላይ በእስር ቤት የቆዩት እስረኞች ሰሞኑን ከፍተኛ ድብደባ ከተፈጸመባቸው በሁዋላ ለተከታታይ ቀናት ምግብ ባለመመገባቸው ህይወታቸው አደጋ ላይ መውደቁን በመግለጽ የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲደርስላቸው አቤት ብለዋል።

እስረኞቹ በጻፉት ደብዳቤ ላይ  ከውጭ የመጡ የመከላከያ ሰራዊት አባላት በፌሮ ክፉኛ እንደደበደቡዋቸውና ህክምና በማጣታቸው ከፍተኛ ስቃይ እየደረሰባቸው መሆኑን ገልጸዋል። ፍርድ ቤት በቀጠሮአቸው ቀን እንዳይቀረቡ መከልከላቸውን ለመቃወም ለበላይ አካላት ደብዳቤ በመጻፋቸው ምክንያት ድብደባ እንደተፈጸመባቸው የገለጹት እስረኞቹ ፣ ጉዳዩን ለቂሊንጦ ዋና አስተዳዳሪ ኦፊሰር አምባየ ስናመለክት ” እስከ መግደል ድረስ እርምጃ ለመውሰድ መብት አለን፣ አርፋችሁ ካልተቀመጣችሁ በጥይት እንቆላችሁዋለን፣ የምግብ ማቆም አድማ እናደርጋለን ብትሉም ለእኛ ደንታችን አይደለም”  በማለት እንደመለሱላቸውና ከዚያን ጊዜ ጀምሮ እየተዛተባቸው መሆኑን ጠቅሰዋል። ለ4 ቀናት ምግብ ማቆማችንን ተከትሎ ማንም ስላልጠየቀን በሞት አፋፍ ላይ እንገኛለን ያሉት እስረኞቹ የኢትዮጵያ ህዝብ እና የሚመለከታቸው አካላት አስቸኳይ እገዛ እንዲያደርግላቸውም እስረኞቹ  ተማጽነዋል።

አበባ እርሻ የሚሰሩ የኬሚካል ጉዳተኞች በርክተዋል የውጪ ምንዛሬ ገቢው 40% ቀነሰ

በከፍተኛ ደረጃ የእርሻ መሬቶችን ወደ አበባ እርሻ ማሳ ለሚቀይሩ ባለሃብቶች በመሸጡ ተቃውሞ የሚሰነዘርበት የኢንቨስትመንት ዘርፍ የዜጎችን ህይወት እየተፈታተነ ነው። በአነስተኛ ክፍያ በአበባ እርሻዎች ውስጥ ተቀጥረው የሚሰሩ ወገኖች ከኬሚካል ጋር በተያያዘ እየደረሰባቸው ያለው የጤና መጓደል አስጊ እንደሆነ አሁንም ድረስ ትኩረት እንደሚፈልግ እየተነገረ ነው።
ለገቢው ልዩ ትኩረት የሚሰጠው መንግስት በበጀት ዓመቱ ከዘርፉ የጠበቀውን ገቢ አለመግኘቱን ተጠቁሟል። ከ2 ነጥብ 1 ቢሊዮን በላይ የአበባ ዘንግ፣ 114ሺ ቶን አትክልት እና 13ሺ ቶን ፍራፍሬ ባለፉት 11 ወራት ወደ ተለያዩ ሀገራት ቢላክም flower farm eesመጠኑ ከእቅድ በታች እንደሆነ ተገልጾዋል። ፋና የኢትዮጵያ  ሆርቲካልቸር ልማት ኤጄንሲን ጠቅሶ እንደዘገበው ወደ ውጪ ከተላኩት የአትክልት ምርቶች ከ212 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል። ገቢው ከእቅዱ ስልሳ በመቶ ብቻ ነው። ኤጀንሲው ለገቢው መቀነስ የአለም ኢኮኖሚ መቀዛቀዝና በአለም አቀፍ ደረጃ የአየር ሁኔታ መለዋወጥ እንደ ምክንያት አቅርቧል።
ከአበባ እርሻ ጋር በተያያዘ በርካታ ዜጎች ለበሽታ መዳረጋቸውና በቂ የጤና ዋስትና እንደሌላቸው በተደጋጋሚ የሚገለጽ ችግር ነው። በአበባ ማበልጸጊያ ድንኳን ውስጥ የሚሰሩ ዜጎች ለኬሚካል ብክለት መጋለጣቸው የከፋ ችግር ከመሆኑም በላይ ከእርሻዎቹ የሚወጡ ፍሳሾች ወራጅ ውሃና ወንዝ ጋር በመቀላቀል አደጋ እያስከተለ ነው። ከዚህም በላይ የአበባ እርሻዎች ከፍተኛ ሃይል ያለው መርዝ ስለሚጠቀሙ መሬቱ ለወደፊቱ እህል እንደማያበቅል ባለሙያዎች በጥናት አረጋግጠው ያቀረቡበት የማይመከር ኢንቨስትመንት እንደሆነ መጠቆሙ አይዘነጋም።

Saturday 20 July 2013

በአንድ ሳምንት ሁለተኛ አደጋ!

“አውሮፕላኑ አየር ላይ እያለ ሊፈነዳ ይችል ነበር”

ethiopian


ከአዲስ አበባ ወደ አክሱም ይጓዝ የነበረ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ረቡዕ ለት በጭንቅ እንዲያርፍ መደረጉ ተገለጸ፡፡ አደጋው ከአምስት ደቂቃ በፊት ቢከሰት ኖሮ አውሮፕላኑ አየር ላይ እያለ ሊፈነዳ ይችል እንደነበር ባለሥልጣናት አስታወቁ፡፡
78 መንገደኞችንና ሠራተኞችን አሣፍሮ ይጓዝ የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ (Bombardier Q400) አውሮፕላን ከክንፎቹ በአንዱ ጭስ መነሣቱን የሚጠቁም ማስጠንቀቂያ በመደወሉ እጅግ አስጨናቂ በሆነ መልኩ እንዲያርፍ መደረጉን ሱዳን ትሪቢዩን ዘግቧል፡፡ ጋዜጣው ስማቸው ከመግለጽ የተቆጠቡ ባለሥልጣንን ጠቅሶ እንደጻፈው አውሮፕላኑ ከማረፉ ከአንድ ደቂቃ በፊት የግራው ክንፍ እየጨሰ መሆኑን ማስጠንቀቂያው ማመልከቱንና አንዱ ሞተር ደግሞ እንደሚገባው ይሰራ እንዳልነበረ ገልጸዋል፡፡

Friday 19 July 2013

ከፍተኛ የሙስና ወንጀል ሲጋለጥ

July 19, 2013

ከኢየሩሳሌም አርአያ
ወ/ሮ አዜብ መስፍን ከአቶ ገ/ዋህድ፣ አቶ ነጋና ምህረተአብ ጋር በመመሳጠር በሶስት መርከብ ስሚንቶ አስጭነው አገር ውስጥ በማስገባት ከፍተኛ የሙስና ወንጀል መፈፀማቸውን ምንጮች አጋለጡ። በተከለከለ ፍራንኮ ቫሉታ ፈቃድ አገር ቤት የገባው ስሚንቶ በመቶ ሚሊዮን የሚቆጠር ትርፍ አዜብና ግብረአበሮቻቸው እንደዛቁበት ያረጋገጡት ምንጮቹ፣ አያይዘውም ጉዳዩ በደህንነት ሹም አቶ ጌታቸው አሰፋ እጅ እንደገባ አስታውቀዋል። በሕገወጥ መንገድ የውጭ ምንዛሪ በከፍተኛ ደረጃ በመመደብና አስፈላጊውን ትእዛዝ በመስጠት እንዲሁም የጥቅም ተካፋይ በመሆን ግንባር ቀደም ሚና የተጫወቱት አዜብ መስፍን ከዚህ ድርጊታቸው በተጨማሪ ከዚህ ቀደም ከስሚንቶው ጋር በተያያዘ ተመስርቶ የነበረውን ክስ እንዲቋረጥ ማድረጋቸውን የጠቆሙት ምንጮች፣ ይህና ሌሎች ተያያዥ የወንጀል ድርጊቶችን የሚያስረዱ ማስረጃዎች በአቶ ጌታቸው እጅ እንደገቡ አረጋግጠዋል። አቶ ነጋ ገ/እግዚያብሄር በኮንትሮባንድ ቀረጥ ሳይከፈልባቸው ወደ አገር ውስጥ ያስገቧቸው የህክምና መሳሪያዎች ተይዘው ክስ ከተመሰረተባቸው በኋላ ክሱ እንዲቋረጥ ያደረጉት አዜብ መሆናቸውን የገለፁት ምንጮቹ፣ በተለያዩ ጊዜያት የገቡና የነጋ ገ/እግዚያብሄር ንብረት የሆኑ ከባድ ተሽከርካሪዎች ያለቀረጥ እንዲገቡ በማድረግ አዜብ መተባበራቸውን አያይዘው ገልፀዋል። ጉዳዩም «ክስ በማቋረጥ..» በሚል በሰነድ ተደግፎና ከሌሎች መሰል ድርጊቶች ጋር ተያይዞ በታሳሪዎች ላይ ክስ የቀረበ ቢሆንም፣ ዋናው ተዋናይ ግን አዜብ ሳይጠየቁ መቅረታቸው አነጋጋሪ መሆኑን ምንጮቹ አልሸሸጉም። ከስሚንቶው ጋር በተያያዘ አስተያየት የጠየኳቸው ታዋቂ የሆኑ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ባለሙያ ፥ « መንግስት ስለ ፍራንኮ ቫሉታ ሕግ አውጥቷል፤ ይህን በመተላለፍ ሶስት መርከብ ስሚንቶን የሚያክል ነገር በታሳሪዎቹ ብቻ ሊፈፀም አይችልም፤ ከዚህ ሕገወጥ ድርጊት በስተጀርባ ትልቅና ቁልፍ ስልጣን ያለው ሰው እጁ እንዳለበት ግልፅ ነው።» ብለዋል።

Thursday 18 July 2013

የኢትዮጵያ ጦር ከባይደዋ መዉጣቱ


የኢትዮጵያ ወታደሮች ከባይደዋ መዉጣታቸዉን አሶሲየትድ ፕረስ ትናንት አመልክቷል። መንግስት መፍትሄ ይፈለጋል ቢልም ወታደሮቹ ከተጠቀሰችዉ ስልታዊት የሶማሊያ ከተማ መዉጣታቸዉም በአፍሪቃ ኅብረት ሰላም አስከባሪዎችና የሶማሊያ መንግስት ወታደሮች ላይ ጫና እንደሚያስከትል እየተነገረ ነዉ።
«ከኢትዮጵያ ወታደሮች የተወሰኑት ከባይደዋ ወጥተዋል፤ አሁንም ግን በአካባቢዉ ወታደሮች ይገኛሉ። ሆኖም ግን ቀስ በቀስ ከመላ ሶማሊያ እንደሚወጡ እርግጥ ነዉ።»

ኢህአዴግ በሩን እንዲከፍት የዓለም ባንክ አዘዘ የማነቂያው ገመድ ከርሯል፤ “ትግሉ ይቀጥላል” ኦባንግ ሜቶ


world-bank


ኢህአዴግ ለሚገዛት ኢትዮጵያ ከፍተኛ መጠን ያለው ዕርዳታ የሚሠጠው የዓለም ባንክ፤ ለዕርዳታና ልማት የሚልከው ገንዘብ ኢህአዴግ የሕዝቡን ሰብዓዊ መብት ለመጣስ ተጠቅሞበታል በሚል ሙሉ ምርመራ እንዲካሄድ አዘዘ፡፡ የባንኩ ውሳኔ ኢህአዴግን የማነቂያው ገመድ እንደሚያከረው ተገለጸ፡፡ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ በተለይ ለጎልጉል በሰጡት መግለጫ “ይህ በጥናት ከምናካሂደው ትግል አንዱ ውጤት ነው፤ ገና ጅማሬ ነው፤ ጠንክረን እንሠራለን” አሉ፡፡
የዓለም ባንክ ለልማት ሥራዎች የሚሰጠው የእርዳታ ገንዘብ በኢትዮጵያ በተለይም በጋምቤላ ክልል የሚኖሩትን ዜጎች ሰብዓዊ መብት በመጣስ ላይ ውሏል በሚል ከዚህ በፊት ክስ ቀርቦበት እንደነበር ይታወሳል፡፡ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ጉዳዩን ከ9 ወራት በፊት በዘገበበት ወቅት ተጠቂዎቹ ዜጎች ያቀረቡትን ማስረጃና የኢንስፔክተር ቡድኑ የሚያደርገውን ምርመራ በዝርዝር ሰፍሮ ነበር፡፡ በወቅቱ ምርመራውን ያደረገው የመርማሪ ቡድን (ኢንስፔክሽን ፓናል) በአካባቢው የሚገኙትን ተጠቂዎች ካነጋገረ በኋላ ለባንኩ የሥራ አመራር ቦርድ በሰጠው ሪፖርት በዕርግጥ የዕርዳታው ገንዘብ በሰብዓዊ መብት ረገጣ ላይ መዋሉን ይፋ አድርጓል፡፡

Wednesday 17 July 2013

የአውሮፓ ፓርላማ ልዑካን በኢትዮጵያ


ፀረ ሽብር የተባለውን ደንብ ነቅፈናል። አንቀጹ የሚያሻማ፣ ግልጽ ባልሆኑ አንቀጾች የተቀመጠ ነው። ሰዎች በዚህ ሳቢያ ራሥረዋል። ስለሆነም የህግ አውጪው ፣ ተርጓሚውና አስፈጻሚው ዘርፍ ፤ ነጻነት በተሃድሶ ለውጥ ሊቀየር ብለን እናስባለን ። በአጠቃላይ በኢትዮጵያ እሥር ቤቶች የታሣሪዎች ይዞታ እንዲታይ የሚል አቋም ነው ያለው ።
ኢትዮጵያን ለ3 ቀናት የጎበኘው የአውሮፓ ፓርላማ የሰብዓዊ መብት ልዑካን ቡድን ጋዜጠኞችና ፖለቲከኞች የተያዙበትን እስርቤት እንዳይጎበኝ ተከለለ ። ከአዲስ አበባ የወጡ ዘገባዎች እንዳመለከቱት ቡድኑ እስር ቤቱን እንዲጎበኝ ፈቃድ አግኝቶ ነበር ። የልዑካን ቡድኑ የኢትዮጵያ መንግሥት የታሰሩትን ጋዜጠኞችና ፖለቲከኞች እንዲፈታ ጠይቋል ። 

Tuesday 16 July 2013

Ethiopia: The Continuing of Deaths and Displacements in Eastern Oromia

HRLHA Fine

HRLHA Urgent Action
July 16, 2013
Public: for immediate Release
In a development relating to HRLHA URGENT ACTION, May 7, 2013, ” Ethiopia: Loss of Lives and Displacement Due to Border Dispute  in Eastern Ethiopia”
HRLHA has learnt that three innocent civilians have been killed and two others wounded in eastern Oromia’s Regional State, in Ethiopia in a violence that involved the Federal Government’s special force known as LIYYU POLICE. According to HRLHA informants, the three dead victims of this most recent attack by the federal Liyyu Police/Special Police that took place in the early morning of July 7, 2013 in the Gaara-Wallo area in Qumbi District of Eastern Hararge Province in Eastern Ethiopia were:
  1. Mr. Ibrahim Henno, 38,
  2. Mr. Mahammed Musa, 26
  3. Mr. Mohammed Yusuf , 27

World Bank Board approves investigation into allegations of bankrolling human rights abuses in Ethiopia

By IDI
July 16, 2013



(July 16, 2013) The World Bank’s Board of Executive Directors has approved a full investigation into whether the Bank has breached its policies in Ethiopia and contributed to a government program of forced population transfers known as ‘villagization.’  The Bank’s move follows the resolution of a five-month standoff with the Ethiopian government, which had publicly threatened in May not to cooperate with the investigation.     
A preliminary report issued by the Bank’s internal watchdog, the Inspection Panel, recommended the investigation in February after receiving a complaint submitted by indigenous people from Ethiopia’s Gambella region.

Monday 15 July 2013

በቂልንጦ እስርቤት የእሰረኞች ደም በድብደባ እንደጎርፍ መፍሰሱን የአይን እማኞች ተናገሩ

ሐምሌ ፰( ስምንት )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና :- አርብ ፣ ሀምሌ 6 2005 ዓም በእነ አቶ ተሻለ ኮርኔ መዝገብ የተከሰሱ 69 የኦሮሞ ተወላጆች ፍርድ ቤት መቅረብ ሲገባቸው፣ ፍርድ ቤት የሚወስዳቸው ፖሊስ ያጣሉ። በቅጽል ስሙ ሻእቢያ እየተባለ የሚጠራውን የእስር ቤቱን ሀላፊ ሲጠይቁት ቀጠሮአቸው ለ4 ወር መራዘሙን ይነግራቸዋል። እስረኞቹም ” ከ2 አመታት በላይ የላፍትህ ታስረን በመጨረሻ ብይን በሚሰጥበት ወቅት ለ4 ወራት ተራዝሟል መባሉ ተገቢ አይደለም”  በማለት ለጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ የሚላክ ፊርማ ማሰባሰብ  ሲጀምሩ ማረሚያ ቤቱ መረጃው ይደርሰውና 69ኙ እሰረኞች በ20 ተከፋፍለው ወደ ተለያዩ የማረሚያ ክፍሎች ወይም ዞኖች እንዲበተኑ ይደረጋል።
አርብ ጧት ሌሎች እስረኞች ወደ ውጭ እንዳይወጡ ከተደረገ በሁዋላ ፣ ሻእቢያ በሚባለው የእስር ቤቱ ሀላፊና ከውጭ በመጡ የፌደራል ፖሊስ አባላት እንዲደበደቡ ይደረጋል። አስተባባሪ ናቸው የተባሉትን 18 እስረኞችን እንደገና በማውጣት በሰደፍና እና በዱላ ከቀጠቀጡዋቸው በሁዋላ 8ቱ ራሳቸውን ሲስቱ ወደ እስር ቤቱ የህክምና ክፍል ይወሰዳሉ።  ችግሩ ከአቅሙ በላይ መሆኑን የእስር ቤቱ የህክም ክፍል በመግለጹ፣ በአምቡላንስ ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል።
የአይን እማኞች ለኢሳት እንደገለጹት እስረኞቹ የተደበደቡበት ቦታ በደም በመጨቅየቱ አርብ እለት በውሀ ሲታጠብ አርፍዷል።

የፌደራል ፖሊስ የግዥ አፈፃፀም ሥርዓት ለሙስና የተጋለጠ መሆኑን የጸረ ሙስና ኮምሽን በጥናት አረጋገጠ

ሐምሌ ፰( ስምንት )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና :-የፌዴራል የሥነምግባርና የጸረ ሙስና ኮምሽን በቅርቡ ባካሄደው የአሰራር ሥርዓት ጥናት በፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የግዥ አፈፃፀም ለሙስና እና ብልሹ አሠራር የተጋለጠ ነው ብሎአል፡፡
በፖሊስ ኮምሽኑ የተጠና የጠቀሜታ ዝርዝር /ስፔስፊኬሽን/ አዘገጃጀት አሰራር አለመኖር፣ ግዥዎችን በዕቅድና
በፕሮግራም አለመፈፀም፣ በጀት መኖሩ ሳይረጋገጥ የግዥ ሂደቶችንማከናወን፣ በግዥ መመሪያው ከተቀመጠው የገንዘብ መጠን በላይ ግዥ መፈፀም እና የጨረታ ኮሚቴው ከግዥ መመሪያውን ተከትሎ አለመሥራት ዋና ዋና ጉድለቶች መሆናቸውን ኮምሽኑ በጥናቱ አረጋግጧል፡፡
የፌደራል መንግሥት የግዥ አፈፃፀም ሥርዓት መመሪያ የጠቀሜታ ዝርዝር /ስፔስፊኬሽን/ በተጠቃሚዎች ዝርዝር ላይ የተመሠረተ ሆኖ ዕቃዎችንና አገልግሎቶችን የሚፈለገውን ለማሟላት ያላቸውን ተፈጥሮ፣ የሚያስገኙትን ውጤት፣ ለመሥሪያ ቤቱ የሚያስገኙትን ጠቀሜታ፣ የአሠራር ባሕሪያቸውንና የታቀደላቸውን ሥራ ለማከናወን ያላቸውን የብቃት ደረጃ የሚያካትት ዝርዝር መግለጫ መዘጋጀት እንዳለበት ይደነግጋል፡፡ ይሁን እንጂ በፌደራል ፖሊስ መሥሪያ ቤት የሚዘጋጁት አንዳንድ የጠቀሜታ ዝርዝሮች  የሚገዙትን ዕቃዎች ወይም አገልግሎቶች በግልጽ የሚያሳዩ ባለመሆናቸው የግዥ ውሳኔዎች ወደአልተፈለጉ አቅጣጫዎች እንዲያጋድሉ በማድረግ የአሠራር ክፍተቶች ሊፈጥሩ እንደሚችሉ ጥናቱ ያሳያል፡፡

Sunday 14 July 2013

Mooraa Yuuniversitii Jimmaa Keessatti Poolisoonni Wayyaanee Reebicha Hammeenyaa Barataa Oromoo Saykoloojii Baratu Irraan Gahaniin Lubbuun Darbuu Gabaafame.


Adoolessa 14,2013 Jimmaa

Mooraa Yuunivarsiitii Jimmaa keessaattii yakkii ajjeechaa Poolisotaa fi dabbaloota Mootummaa Wayyaanee fi EPRDF’n barataa Oromoo irraatti rawwatame.
Poolisonnii fi dabbaalloonnii sirnaa Wayyaanee EPRDF’n durfaman mooraa Yuunivarsiitii Jimmaa keessaatti Ilmaan Oromoo adamsanii ajjeesaanii dhuksuuf yaalii torbee tokkoo oliif godhaniyyuu ciminaa sabboontotaa Qeerroo baratootaa Oromoo if irraa eegaa turan.
Akka kanaan barataa Faasil Huseen Umar Barataa Saayikooloojii Waggaa 2ffaa bakkii dhalootaa isaa Godinaa Baalee kan ta’ee Adooleessaa 7/2013 galgala keessaa sa’aa 2;30 irraatti utuu Yuunivarsiitii Jimmaa karraa guddaa karaa dhihaa gara mooraatti seenaa jiruu humnotaa Poolisaa karraa irraa Jiraniin qabamee Wajjiraa Poolisaa Mooraa Yuunivarsiitii Jimmaa keessaatti argamuu biroo hogganaa wajjiraa Poolisaa mooraa Yuunivarsiitii Jimmaa Kaliid Abbaa Tamaamiitti geeffaamuun humnotaa tikaa ,dabbaalootaa fi hogganaa pooliisii mooraa Yuunivarsiitii Jimmaan reebbichaan humnaa olii irraatti rawwaatame,

Saturday 13 July 2013

450 ሚ.ብር ሙስና ተጠርጣሪዎች ፍ/ቤት ቀረቡ

Written by  አለማየሁ አንበሴ

በኤሌክትሪክ እቃዎች ግዢ ላይ ሙስና በመፈፀም መንግስትን (ከ450.ሚ ብር) በላይ አሳጥተውታል ተብለው ሰሞኑን የታሰሩ ዘጠኝ የኤሌትሪክ ሃይል ኮርፖሬሽን የስራ ሃላፊዎች ላይ ፀረ ሙስና ኮሚሽን ተጨማሪ ምርመራ እንዲያካሂድ ተፈቀደለት፡፡ ተጠርጣሪዎቹ በሁለት የምርመራ መዝገብ ተካተው የቀረቡ ሲሆን፤ በአንደኛው መዝገብ የኮርፖሬሽኑ ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ብርሃኔ አበበ እና የቴክኒክ ክፍል ቡድን መሪ አቶ መኮንን ብርሃኔ ተሰማ ተመዝግበዋል፡፡ በሁለኛው መዝገብ ስር የተካተቱት 7 ግለሰቦች በኮርፖሬሽኑ የሃገር አቀፍ የኤሌክትሪክ ሃይል አቅርቦት ፕሮግራም ስራ አስፈፃሚ አቶ ሽፈራው ተሊላ፣ የኢንጂነሪንግ ክፍል ሃላፊ አቶ ሚሊዮን ማቱሳላ፣ የሠፕላይቼይን ሃላፊ አቶ ዳንኤል ገ/ስላሴ፣ የኢንጅሪንግ ፕሮሰሲንግ የስራ ሂደት ተወካይ አቶ ሠመረ ሃሳቤ እንዲሁም የጨረታ ኮሚቴ አባላት አቶ ፋሪስ አደም፣ አቶ ብሩክ ተገኘ እና አቶ ጌታቸው አዳነ የተሰኙ ግለሰቦች ናቸው፡፡
የኮሚሽኑ የምርመራ ቡድን፤ ግለሰቦቹ የተጠረጠሩበትን ጉዳይ ለፍርድ ቤቱ እንዳቀረበው፤ በአንደኛው መዝገብ የተካተቱት አቶ መስፍን ብርሃኔ፣ የስልጣን ውክልና ሳይኖራቸው እና የኮርፖሬሽኑን ይሁንታ ሳያገኙ ከሪዘርቭ ባንክ ኦፍ እንዲያ እ.ኤ.አ ሚያዚያ 10 ቀን 2009 ዓ.ም በፃፉት ደብዳቤ፤ የግዢ ውሉን ተቀባይነት ማረጋገጫ በመስጠታቸው እንዲሁም ኮርፖሬሽኑ አዳዲስ 3520 ትራንስፎርመሮች ለሀገሪቱ የሃይል አቅርቦት መገዛት አለበት ብሎ ቢያቅድም አሮጌና ያገለገሉ ትራንስፎርመሮች ባልተገባ የግዢ አካሄድ እንዲገዙ ማድረጋቸው የሚለው ነው፡፡ በአቶ መኮንን ብርሃኔ ላይ የቀረበው የወንጀል ጭብጥ ደግሞ የተገዙትን ትራንስፎርመሮች መመርመር ዋነኛ ተግባራቸው ሆኖ ሳለ፣ በአቶ መስፍን ብርሃኔ የተዘጋጀውን ግዢና ውል እንደወረደ በመቀበል ኮርፖሬሽኑ ወይም መንግስት ከ17 ሚሊዮን ዶላር በላይ እንዲያጣ አድርገዋል የሚል ነው፡፡ በሁለኛው መዝገብ የካተቱት አቶ ሽፈራው ተሊላ እንዲሁ የስልጣን ውክልና ሳይኖራቸው እና የኮርፖሬሽኑን ፍቃድ ሳያገኙ በሪዘርቭ ባንክ ኦፍ ኢንዲያ እሣቸውም የውሉን ማረጋገጫ ደብዳቤ ጽፈዋል የሚል የወንጀል ጭብጥ ቀርቦባቸዋል፡፡

A Boeing 787 Dreamliner operated by Ethiopian Airlines caught fire at Heathrow airport


heathrow1_130712
Boeing said it was working to understand the cause of the fire.
July 12, 2013 (ABC) — A Boeing 787 Dreamliner operated by Ethiopian Airlines has caught fire at Britain’s Heathrow airport.
It is a fresh blow for the US planemaker which earlier this year was forced to ground the new planes for three months after battery fires.
Boeing shares tumbled by as much as 7 per cent after television footage showed the Dreamliner surrounded by foam used by firefighters at Heathrow.
Heathrow briefly closed both its runways to deal with the fire, which broke out while the aircraft was parked at a remote stand. There were no passengers aboard the plane.
Television footage showed an area on the fuselage in front of the tail that appeared to be scorched.
It was not clear if the fire was related to the batteries which were the cause of the previous fires on the Dreamliner.

ድሃው ሕዝብ ጉዳዩን ማስፈጸም አይችልም "ጉቦኝነት 44% ሆኗል"


city


“ዕድገት”፣ “ትራንስፎርሜሽን”፣ “ህዳሴ”፣ “የመለስ ውርስ (ሌጋሲ)”፣ … በሚመሯት ኢትዮጵያ ሙስና እየከፋ መሄዱ ታወቀ፤ ከመቶ ሰዎች ውስጥ ከ40 በላይ የሚሆኑት ጉቦ የሚሰጡ መሆናቸውን አስታወቁ፡፡
ሰሞኑን ዓለምአቀፉ የግልጽነት ድርጅት (Transparency International) ያወጣው መረጃ እንደሚያመለክተው በርካታ የአፍሪካ አገራት በሙስና “መበስበሳቸውን” ከእነዚህም መካከል ኢትዮጵያ ከቀዳሚዎቹ አገራት መካከል እንደምትገኝ ዘግቧል፡፡
ከዚህ በፊት በያዝነው ዓመት ጥር ወር የሙስና አደጋ የተጋረጠባቸው አገራትን ዝርዝርና የአደጋውን መጠን በሰባት ደረጃ በመከፋፈል ይኸው ድርጅት ባወጣበት ጊዜ ኢትዮጵያን በከፍተኛ የሙስና አደጋ ውስጥ ከሚገኙ አገራት ዝርዝር ውስጥ አስገብቷት ነበር፡፡ በዚህ ዘገባ መሠረት በሙስና የተዘፈቁትን አገራት በመከፋፈል ባስቀመጠው ባለዘጠኝ መዘርዝር ውስጥ ኢትዮጵያ ከመጨረሻ ሁለተኛው ውስጥ አካትቷታል፡፡

Wednesday 10 July 2013

የኢትዮጵያ ፀረ ሽብር አዋጅ መሻሻል ለምን?

July 10, 2013

አዘጋጅ Zone 9
በሚኪያስ በቀለ
Any law that uplifts human personality is just. Any law that degrades human personality is unjust. One has not only a legal but a moral responsibility to obey just laws. Conversely, one has a moral responsibility to disobey unjust laws… for an unjust law is no law at all.
Dr. Martin Luther King
የመንግሥት ወይስ የሕዝብ ሕግ?
በኢትዮጵያ ውስጥ የፀረ ሽብር አዋጅ የወጣው በ2001 ዓ.ም ላይ ሲሆን የአዋጁ ረቂቅ የተለያዩ የአለም ዓቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ደርጅቶች እና የተቃዋሚ ፓርቲዎች አዋጁ የዜጎችን የሰብኣዊ መብቶች አደጋ ውስጥ ስለሚከት መስተካከል እንደሚኖርበት ድምፃቸውን አሰምተው ነበር፡፡ ነገር ግን መንግሥት ትችቶቹን ከቋፍ ሳይከት አዋጁን በ2001ዓ.ም ከ547 የፓርላማ አባላቶቿ ውስጥ 378ቱ በተገኙበት በ268 የአዎንታ ድምጽ፣ በ91 ተቃውሞ እና በ1 ድምፀ ተአቅቦ የፀረ ሽብር አዋጅ ቁጥር 652/2001 ኅብረተሰቡን ከአደጋ ለመጠበቅ በሚል አወዛጋቢውን ሕግ አውጥቶ ማስፈጸም ጀምሯል፡፡
Zone9 young Ethiopian bloggers
አዋጁ በወጣበት ቀን “ባለራዕዩ” የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስቴት መለስ ዜናዌ የአዋጁን ትክክለኛነት (Ligitimacy) ለፓርላማው ሲያብራሩ “… አዋጁን ስናረቀቅ ከአሜሪካ፣ ከእንግሊዝ እና ከአውሮፓ አገራት ጥሩ ጥሩውን ቃል በቃል….ለምሳሌ በነዚህ ሃገራት ባለው ሕግ አሸባሪ ብሎ የመፈረጅ ሥልጣን የሕግ አስፈፃሚው ሲሆን እኛ ግን የሕግ አውጪው ሥልጣን እንዲሆን አድርገናል…” ብለው ነበር፡፡ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስቴር በዓለማችን የሕግ የበላይነት ከሰፈነባቸው አገራት የፀረ ሽብር አዋጁን “ቃል በቃል” መገልበጣቸው ሕጉን ትክክለኛ ሊያስብለው እንደሚችል ገልጸዋል፡፡ ለሰው ልጆች ሁሉ የሚሠራ የተፈጥሮ ሕግ (Universal law) እንደመኖሩ አንድ ሕግ ሲወጣ ሀገሪቷ ካላት ሁኔታ እና በሕጉ ከሚተዳደሩት ማኅበረሰቦች አንፃር መሆን እንዳለበት (Capable of being complied with) በማወቅ ይሁን ባለማወቅ ጠ/ሚኒስትሩ የዘነጉት መሠረታዊ የሕግ አወጣጥ መርሕ ነው፡፡ የሰው ልጅ የመኖር (የሕ.መ.አ.15*) እና ከማንኛውን የአካል አደጋዎች የመጠበቅ (የሕ.መ.አ.16*) በዓለማችን ላይ ሁሉ ዕኩል የሚሠሩ የተፈጥሯያዊ መብቶች አሉት፡፡ ነገር ግን እነዚህን መብቶች ለመጣስ በየሃገራቱ ብቻ አይደለም በየኅብረተሰቡ የተለያዩ አደጋዎች እንደመኖራቸው መብቶቹን ለማስጠበቅ የሚወጡት ሕጎች (እንደ ፀረ ሽብር ሕግ) ከቦታ ቦታ እና ከጊዜ ጊዜ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ የተለያዩ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡

Monday 8 July 2013

በጋሞጎፋ ዞን በተነሳው ተቃውሞ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ታሰሩ ብዙዎችም ተደበደቡ

ሐምሌ ፩( አንድ )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና :-እሁድ ሰኔ 30፣ 2005 ዓም በደቡብ ክልል በጋሞ ጎፋ ዞን በቁጫ ወረዳ በሰላም በር ከተማና አካባቢዋ የሚኖሩ ከ7 ሺ በላይ ነዋሪዎች፣ የታሰሩ መሪዎቻችን ይፈቱትልን የሚል ጥያቄያቸውን በወረዳ ጽህፈት ቤት ተገኝተው ለማቅረብ በተጓዙበት ወቅት የዞንና የወረዳ ፖሊሶች በነዋሪዎቹ ላይ ድበደባ መፈጸማቸውን 300 የሚሆኑትን   ደግሞ ማሰራቸውን ያነጋገርናቸው ሰዎች ገልጸዋል።
አንዳንድ ቤተሰቦች ለኢሳት እንደገለጹት ፖሊሶች እድሜያቸው ከ13 አመት በላይ የሆኑ ልጃገረዶችንና ወንዶችን ሳይቀር ከቤታቸው እያወጡ በመደብደብ አስረዋቸዋል።  አቶ ብርሀኑ የተባሉ ነዋሪ ፖሊሶች የፈጸሙት ድርጊት ጨካኝ በሚባለው የደረግ ስርአት ጊዜ እንኳን ያልታየ ነው ብለዋል ። የችግሩን አሳሳቢነት ለክልል ባለስልጣናት ለማስረዳት  አዋሳ ከሚገኙት የአገር ሽማግሌዎች መካከል አንዱ የሆኑት አቶ መሰቦ ማዳልጮ  እንደተናገሩት ፖሊሶቹ እርምጃውን የወሰዱት ጥያቄያቸውን ሰላማዊ በሆነ መንገድ ለማቅረብ በመሰባሰብ ላይ በነበሩበት ጊዜ ነው ።
አንድ ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ የእስረኞች ጠባቂ ፖሊስ እንደተናገረው  300 የሚሆኑ እስረኞች በአንድ ክፍል ውስጥ  ታጉረው የሚገኙ ሲሆን፣ ፖሊስ በዛሬው እለት ፍርድ ቤት ቢያቀርባቸውም፣ እስረኞቹ ግን በወረዳው ፍርድ ቤት ላይ እምነት የለንም በሚል ጥለው መውጣታቸውን ገልጿል።  በድብደባው ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው ወጣቶች ህክምና እንደተከለከሉም ተናግሯል።

Sunday 7 July 2013

Al Jazeera The Stream: We Appreciate Al Jazeera for Airing Oromo’s Persecution in Ethiopia

Petition by Dawaa Oromoo | July 7, 2013

Oromo, a single largest [over 40 million population] ethnic group in Ethiopia, is under repression of successive Ethiopian regimes for more than a century. Generally speaking, Ethiopia is a prison of Oromo people. Over the last 130 years, in Ethiopia, the power is under two minority ethnic groups [namely, the Amhara and Tigre]. The Oromo and other southern nations (Ogaden, Gambela, Afar, Sidama, etc) repressed by the northern, better known as Abyssinian [Amhara and Tigre] regimes. The Oromo people are uniquely targeted by consecutive Ethiopian regimes because of its resources, geographic strategy, and fear from its majority in number.
Oromos are languishing countless human right abuses and yet untold stories of persecution. As human right activists, we are advocating for the God’s given right to human being and its dignity as the United Nations identified in its The Universal Declaration of Human Rights :

Saturday 6 July 2013

በረከት ስምዖን አደጉ ወይስ ተገፉ?

ወርቅነህ ገበየሁ ለምን ወደ ትራንስፖርት ሚኒስትርነት?

workneh and bereket


ሰሞኑንን ይፋ የሆነውን የአዲስ የሚኒስትሮችና የ”ከፍተኛ” ባለሥልጣናት ሹመት ተከትሎ ከውስጥም ከውጭም የተለያዩ አስተያየቶች እየተሰነዘሩ ነው። ጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ሹመቱን ይፋ ከማድረጋቸው በፊት ሪፖርተር “ምንጮቼ ነገሩኝ” በማለት አቶ በረከት ስምዖንን የደህንነት አማካሪ ሚኒስትር የሚያደርጋቸው አዲስ ሹመት እንደሚሰጣቸው ዘግቦ ነበር። ይህንኑ ዜና ተከትሎ “ኢትዮጵያ በኦፊሴል በኤርትራ መመራት ጀመረች” በማለት ቅድመ አስተያየት የሰነዘሩ ጥቂት አልነበሩም።
ሚዲያውን መዳፋቸው ስር አኑረው የቆዩት አቶ በረከት ከመንግስት ኮሙኒኬሽን ሚኒስትርነታቸው ተነስተው የጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያም የፖሊሲና ጥናት አማካሪ ሚኒስትር ተደርገው መሾማቸው “በረከት አደጉ ወይስ ተገፉ?” የሚል ጥያቄ አስነስቷል።
ከመለስ ህልፈት በኋላ ኢህአዴግ ውስጥ ጉልህ ሚና እንዳላቸው ያሳዩት አቶ በረከት ከድርጅታቸው ይሁንታ ውጪ “አቶ ሃይለማርያም ጠ/ሚኒስትር ይሆናሉ። የሚቀረው የስርዓት ማሟላት ጉዳይ ነው” ማለታቸው  የህወሃትና የኦህዴድ ሰዎችን ክፉኛ አበሳጭቶ እንደነበር የሚያስታውሱ አስተያየት ሰጪዎች “አቶ በረከት አማካሪ ሆነው ወደ ጠ/ሚኒስትር ቢሮ መዛወራቸው ከኢህአዴግ ባህሪ አንጻር የመገፋት ወይም ስራ አልባ የማድረግና ከቀጥተኛ ተሳታፊነት የመታቀብ ያህል ነው” ባይ ናቸው።

Tuesday 2 July 2013

Atrocious Torture and Inhuman Treatment in Ethiopia…part 1 to 4


July 2, 2013
Severe Atrocious Torture and Inhuman Treatment in Ethiopia is continuing on innocent human kind.
This Video (with four parts) is a testimony of a person who was detained and tortured by the tyrannical regime in Ethiopia. He was government employee worker, and continuously detained and in three prison centers taken out from his room by government Federal security police at night without any legal letter. He was detained almost for 2 years and just simply released from prison without presenting him to the court.
His father who was a teacher was also killed by Ethiopian Federal security police at school some years back. This young man was arbitrarily detained with suspect as he is against government and may be terrorist. His only mother had no information where he is and was searching him for the last two years over the country.

Monday 1 July 2013

መንግስት በእስራኤል አገር የሰለጠኑ የደህንነት ሀይሎችን አሰማራ

ሰኔ ፳፬ (ሃያ አራት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና :-የኢትዮጵያ የብሄራዊ ጸጥታና  ደህንነት መስሪያ ቤት በእስራኤል አገር በታል አራድ ኔጊቭ ማሰልጠኛ ጣቢያ ያሰለጠናቸው  987 የደህንነት ሰራተኞች በመላ አገሪቱ በሚገኙ 572 ታላላቅ መስጊዶች እና በቴሌኮሚኒኬሽን መስሪያ ቤት ማሰማራቱን ከደህንነት መስሪያ ቤት ያገኘነው መረጃ አመልክቷል ፡፡
ከሰልጣኞች መካከል 11 ዱ ብቻ የእስልምና እምነት ተከታዮች ሲሆኑ ቀሪዎቹ አረብኛ  አቀላጥፈው የሚናገሩ ፣ ቁራንን በስርዓት የተማሩ እና እስልምናን ስርዓቶች ሙሉ በሙሉ የሚፈጽሙ ናቸው፡፡
ቀሪዎቹ ሰልጣኞች በቴሌ ኮሚኒኬሸን መስሪያ ቤት የተመደቡ ሲሆን ሙሉ ለሙሉ በስልክ ጠለፋ  ስራ ላይ ይሰማራሉ፡፡ ከሰልጣኞች መካከል 631 ዱ የትግራይ ብሄር ተወላጆች ሲሆኑ፣ በትምህርት ደረጃም የ2002 ምሩቃን በብዛት ይገኙበታል።
በቴሌ የተቀጠሩት አዲሶቹ የደህንነት ሰራተኞች መንግስት ከፈቀደላቸው ውጭ ሌላ የስልክ ግንኙነት የተጠቀሙትን ሚኒስትሮች በድምጽ እንዲለዩ በተሰጣቸው ፈተና መሰረት የተወሰኑ ሚኒስትሮችን ስም ዘርዝረው አቅርበዋል።

Eebba barattoota Yuunivarsiitii Mattuu irratti diddaa Qeerroo irraa mudateen Wayyaaneen rifaatii keessa bu’e


Waxabajjii 30,2013 Mattuu
Mootummaan Wayyaaneetti diddaan barattoota Yuunivarsiitii Mattuu bara guutuu itti jabaachaa kan ture guyyaa eebbaa irratti itti jabaachuun mootummaa Wayyaanee rifaatii guddaa keessa seensise.Yuunivarsiitii Mattuu keessatti barattootni oromoo gurmuun walitti dhufuun sirbawwan gootummaa fi xiiqii diina waliin wal qabanii jiraachuu kan weellisan yoommuu tahu uummatni eebbaaf Yuunivarsiitii Mattuu deeme gootummaa ilmaan isaaniitti hedduu boonuun barattoota waliin makamuun sirbawwan gootummaa sirbanii jiran.Mootummaan wayyaanee gocha kanaan kan baarage waraana hedduumminaan Yuunivarsiitii keessa seensisuun barattootaa fi uummata nagaa doorsisuu irratti argama.Barattootni oromoo gamtaadhaan walitti dhufuun jala bultii eebbaa irratti sirba Eebbisaa Addunyaa EENYUSHEEN DAANGAA OROMOO LIXXU IRRA EJJETTEE MORMA ISHEE HIN KUTTUU jedhu sirbuun bulchinsa Yuunivarsiitii,Waraana wayyaanee fi basaastota rifaatii guddaa keessa buusisanii jiran.Mootummaan wayyaanee dhiibbaa kamuu taasisu diddaan jabaatee akka itti fufu qeerroon Yuunivarsiitii Mattuu gabaasee jira.

አቶ ስዬ በተመድ ተቀጠሩ

June 30, 2013

ከኢየሩሳሌም አርአያ
አቶ ስዬ አብርሃ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰላም አሰከባሪ ተቋም ውስጥ በወታደራዊ አማካሪነት በጥሩ ደመወዝ መቀጠራቸውን ምንጮች ጠቆሙ። በሙስና ወንጀል ተከሰው ከወንድሞቻቸው ጋር ለስድስት አመት ታስረው የተፈቱት ስዬ በተፈቱ ማግስት የአሜሪካን ድምፅ ራዲዬን ጨምሮ ለተለያዩ መገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ « ፖለቲካ ከልጅነቴ ጥርሴን የነቀልኩበትና አብዛኛው እድሜዬን ያሳለፍኩበት በመሆኑ ከትግሉ መድረክ ልርቅ ጨርሶ አልችልም» በማለት አስረግጠው መናገራቸውን እነዚሁ ወገኖች ያስታውሳሉ። «መድረክ» የሚል የፖለቲካ ስብስብ ከፈጠሩና የአንድነት አባል መሆናቸውን በይፋ ካወጁ በኋላ «ለትምህርት» በሚል ወደ አሜሪካ የመጡት ስዬ ከአንድነት ፓርቲ ሪፖርት እንዲያደርጉ የቀረበላቸውን ተደጋጋሚ ጥያቄና ማስጠንቀቂያ ችላ በማለት መልስ ለመስጠት ፈቃደኛ ሳይሆኑ መቅረታቸውን አመልክተዋል። በመጨረሻ « በቅርቡ አገር ቤት ተመልሼ ትግሌን እቀጥላለሁ » ማለታቸውን ያልሸሸጉት ምንጮቹ ስዬ ይህን በተናገሩ ሰሞን በሲያትል በተደረገ ስብሰባ ላይ « ለ21 አመት የተጀመረውን ልማትና ዲሞክራሲ እናስቀጥላለን» በማለት ብዙዎችን አንገት ያስደፋና ያሳዘነ ንግግር ማሰማታቸውን አስታውሰዋል። በአቶ መለስ ዜናዊ ሞት የተሰማቸውን ሃዘን ለመግለፅ አደባባይ መውጣታቸው ብሎም «ያሰራቸውን ስርአት ዲሞክራሲያዊ » አድርገው ለማቅረብ መሞከራቸው አስገራሚ ነበር ብለዋል።