Sunday 30 June 2013

በከፍተኛ ሙስና የተዘፈቀው መከላከያ ሂሳቡ እንዳይመረመር ታዘዘ


-የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት በሚያዚያ ወር 2005 ዓ.ም ባቀረበው ሪፖርት የመከላከያና የደህንነት ተቋማት
የፋይናንስ አያያዝ ከፍተኛ ችግር እንዳለበት ማመልከቱን ተከትሎ በየመ/ቤቶቹ የተነሳውን ቅሬታ ለመፍታት በቀጥታ
እነዚህን ተቋማት በተለየ ሁኔታ ኦዲት ለማድረግ የሚያስችል አዋጅ እየተረቀቀ መሆኑ ተጠቆመ፡፡
የፌዴራል ዋና ኦዲተር አቶ ገመቹ ዱቢሶ ሚያዚያ 22 ቀን 2005 ዓ.ም ለፓርላማው ባቀረቡት የ2004 ዓ.ም
የፌዴራል የመንግስት መ/ቤቶች የሂሳብ አያያዝ ሪፖርት በተለይ በዘጠኝ መ/ቤቶች 3 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር
ባልተሟላ ሰነድ ወጪ ሆኖ መገኘቱን፤ ከዚህ ውስጥ 3 ነጥብ 2 ቢሊየን ብሩ የመከላከያ ሚኒስቴር መሆኑን
መግለጻቸው ይታወሳል፡፡
እነዚህ ተቋማት ላወጡት ገንዘብ ትክክለኛ ማስረጃ እንዲያቀርቡ ተጠይቀውም ማቅረብ አለመቻላቸውን ለፓርላማው
ሪፖርት ካደረጉ በኋላ በተለይ የመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ሲራጅ ፈረጌሳን ጨምሮ የተለያዩ ሹማምንት ሪፖርቱን
በአደባባይ እስከማብጠልጠል የደረሰ ትችት ሲያቀርቡ ተደምጠዋል፡፡ ዋናው መከራከሪያቸውም የመከላከያ ወጪ ሚስጢር
ነው የሚል ነበር፡፡

Friday 28 June 2013

“መቶ ሚልዮን የሰረቁና ያስዘረፉ፤ 10ሺህ ብር የሰረቀውን ሲያገላብጡት ሲያስፈራሩት ይታያሉ” – ስብሃት ነጋ (አዲስ ቃለ-ምልልስ)


(በቀጣይ ለዘ-ሐበሻ አንባቢዎች ያቀረብነው ቃለ ምልልስ አቶ ስብሃት ነጋ ሰንደቅ ለሚባለው ጋዜጣ የሰጡትን ቃለ ምልልስ ነው። ቃለ ምልልሱ ዛሬ በኢትዮጵያ በታተመው ጋዜጣ ላይ ታትሞ ተሰራጭቷል። ጥያቄዎቹ በሰሞናዊዎቹ በሙስና እና በአባይ ጉዳይ ያተኩራሉ። ለግንዛቤዎ በሚል እንደወረደ አቅርበነዋል”")
ሰንደቅ፡- ባለፉት ስርዓቶች ሙስና እንደ አሁኑ ብዙ ጫጫታ አይሰማበትም ነበር። ለምን አሁን?
አቶ ስብሀት ነጋ፡- ትክክል ነህ። ምክንያቱም በፊውዳሉ ስርዓት መሬቱም ጉልበቱም የባላባቶቹ ንብረት ስለነበረ ቀጣፊ የሚባለው ጭሰኛ ነበር። “ቅጥፈቱም” ለባላባቶች ከሚያርሰው መሬት ትንሽ ለሆዱ የሚሆን በቆሎ ከዘራበት ለምን ቦሎቄ አልዘራህም ተብሎ በቦሎቄ ሂሳብ ይቀጣል። የመንግስት ሰራተኛ የመንግስት ገንዘብ ከሰረቀ ግን ጐደለበት ነበር የሚባለው። በደርጉ ቢሮክራቲክ ሶሻሊዝም ስርዓትም ቢሆን የከተማ ንብረት በመሉ በእጁ ስለነበረ የተገኘችው እንደፈለገ ነበር፤ ለራሱም ለቤተሰቦቹም ሲጠቀምበት የነበረው። ስለዚህ ሁለቱም ሃብት ፈጣሪዎችም አልነበሩም የተፈጠረው ሃብትም በመሰረቱ የራሳቸው ነበር። አሁን በመንግስትም በገበሬም በግሉ ባለሀብትም በፍጥነት ሃብት እየተፈጠረ እያለ ከስርዓቱ ጋር የማይሄድ ሙስና እያጋጠመ ነው።

Thursday 27 June 2013

The Stream Oromos seek justice in Ethiopia

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚኖሩ የኦሮሞ ተወላጆች ተፈናቀልን አሉ


ቀድሞ በኦሮሚያ ክልል በምሥራቅ ወለጋ ሊሙ ወረዳ ነዋሪ የነበሩና በኋላ ወደ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ገብተው በቤሌ ጃጐንፎይ ወረዳ የተዛወሩ 44 አባወራዎች፣ ‹‹በመንደር ማሰባሰብ›› ስም በ2003 ዓ.ም. የክልሉ መንግሥት እንዳፈናቀላቸው በተወካዮቻቸው አማካይነት አስታወቁ፡፡ 
ተፈናቃዮቹ እንደገለጹት፣ ለቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ድንበር አዋሳኝ በነበረውና በ2000 ዓ.ም. ወደ ክልሉ በተቀላቀለው ይዞታቸው ላይ ለሃያ አምስት ዓመታት ኖረዋል፡፡ በወቅቱ የኦሮሚያ ክልል ሰብስቦ ካወያያቸው በኋላ ወደ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ መቀላቀላቸውን እንዳሳወቃቸውና ጉዳዩ የመንግሥት ውሳኔን የተከተለ በመሆኑ፣ ነዋሪዎቹ ወደ ቤኒሻንጉል ክልል መቀላቀላቸውን ይናገራሉ፡፡ ከነዋሪዎቹ ጋር የተደረገው ውይይትም ሰላማዊ መሆኑን፣ ነገር ግን ወደ ቤኒሻንጉል ክልል እንዲካለሉ ከመደረጉ በፊት ድንበርተኛ እንደመሆናቸው ግጭቶች ይከሰቱ እንደነበር አስረድተዋል፡፡ 
ምንም እንኳ ወደ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ሲከለሉ አካሄዱ በውይይትና በማሳመን የነበረ ቢሆንም፣ ለመንደር ማሰባሰብ በሚል የክልሉ መንግሥት በ2003 ዓ.ም. ፈጽሞ ሳያሳውቃቸው ግብር ከሚገብሩበት መሬታቸው ላይ ማስነሳት መጀመሩን አስታውሰዋል፡፡
ከተፈናቀሉበት ጊዜ ጀምሮ ለቀበሌ፣ ለወረዳ፣ ለዞንና ለሚመለከታቸው የመንግሥት ተቋማት አቤቱታቸውን ሲያቀርቡ ቢቆዩም፣ ዛሬም አቤቱታቸው ሰሚ ጆሮ አላገኘም ይላሉ፡፡ ለረዥም ወራት ቤትና መሬት አልባ ሆነው የነበራቸውን ሀብትና ንብረት ሸጠው በመጨረስ የዕለት ጉርስ እስከመቸገር መድረሳቸውን ይናገራሉ፡፡ 
‹‹በ2003 ዓ.ም. ሳናርስ ቀረን፤ ነገሮች ይለወጣሉ ብለን ብናስብም በ2004 ዓ.ም. እንዲሁ ስንንከራተት ጊዜው አለቀ፤›› የሚሉት ተፈናቃዮቹ፣ በሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ተደጋጋሚ ውይይት ተደርጎ ለተፈናቀሉት አባወራዎች ተለዋጭ መሬት እንዲሰጣቸው ቀነ ገደብ ቢያዝም፣ ውሳኔው ተግባራዊ ሳይሆን መቅረቱን አስረድተዋል፡፡ 

Tuesday 25 June 2013

Oromos seek justice in Ethiopia

Why is the largest ethnic group in Ethiopia also one of the most persecuted?

On Tuesday, June 25 at 19:30 GMT on The Stream, Aljazeera TV 
In USA, Eastern time:   3:30 PM 
oromoseekjustice
Ethiopians belonging to the Oromia ethnic pray for the souls of 63 young Oromo men who died at sea while trying to cross illegally from Libya to Italian Lampedusa island the week before, at the UAE (United Arab Emirates) Red Crescent refugee camp near the border crossing with Libya at Ras Jdir, Tunisia, 15 April 2011. EPA/AMEL PAIN
The Oromo people make up about 40 per cent of Ethiopia’s population, yet face widespread discrimination and have long been targeted by the government. So what should be done to stop the marginalization of the Oromos and end Ethiopia’s internal ethnic divide?

ኦባንግ ከቴላቪቭ ባለስልጣናት ጋር ይመክራሉ

“መኖር አለ፣ መሞት አለና ወደ ህሊናችን እንመለስ"

obang-in-israel-edited


እስራኤል ኢትዮጵያ ውስጥ በህዝብ ፍላጎት የሚመረጥ የተረጋጋ መንግስት እንዲቆም ከመቼውም ጊዜ በላይ የምትንቀሳቀስበት ወቅት ላይ መሆኗን ለማሳሰብ በነገው እለት ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር እንደሚመክሩ አቶ ኦባንግ ሜቶ አስታወቁ። የሒብሩ ዩኒቨርስቲ ምሁራንና ማህበረሰብ ለአቶ ኦባንግ መልክት ድጋፍ እንዲያደርጉ የሚጠይቅ ንግግር ያደርጋሉ። በእስራኤል የሚኖሩ ስደተኛ ወገኖችን አስመልክቶ ቃል እንደተገባላቸውም አመልክተዋል። አቶ ሳሙኤል አለባቸው “መኖርና መሞት ስላለ ወደ ህሊናችን ልንመለስ ይገባል” አሉ።
የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ዋና ዳይሬክተር የአሜሪካ እንደራሴ (ኮንግረንስማን) ክሪስ ስሚዝ በመሩት የምክክር ሸንጎ ላይ ንግግርና ማብራሪያ ካሰሙ በኋላ ወዲያውኑ በቀጥታ ወደ እስራኤል አምርተው ነበር። ለሁለት ጉዳዮች ወደ እስራኤል ያመሩት አቶ ኦባንግ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ ከእስራኤል ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር በነገው ዕለት እንደሚመክሩ ለጎልጉል ሲያስታውቁ ስለሚናገሩበት ጉዳይም ፍንጭ ሰጥተዋል።

Monday 24 June 2013

በ2005 ዓም ኢትዮጵያ ከወደቁ አገራት ምድብ ተመደበች



ሰኔ ፲፯ (አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና :-ፎሬን ፖሊሲ መጽሄት በእያመቱ በሚያወጣው የወደቁ አገራት ሪፖርት ወይም በእንግሊዝኛው አጠራር ፌልድ ስቴትስ ኢንዴክስ ኢትዮጵያ እንደ አለፉት አመታት ሁሉ ዘንድሮው የወደቁ ወይም በመውደቅ ላይ ካሉ 20 አገራት መካከል አንዷ ሆና ተመድባለች። የህዝብ ቁጥር ፣ የስደተኛ ቁጥር፣ የህዝብ ብሶት፣ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት፣ ያልተመጣጠነ እድገት፣ የመንግስት ህጋዊነት፣ ማህበራዊ አገልግሎት፣ የደህንነት ጥበቃ፣ የሊህቃን መከፋፈልና የውጭ ጣልቃ ገብነት የሚሉት መስፈርቶች ተገምግዋል።
በዚህም መሰረት ከ1 እስከ 20 ያሉት አገራት ህልውናቸው  አስተማማኝ ያልሆነ ከፍተኛ ችግር ያለባቸው ተብለው ተመድበዋል። ሶማሊያ ቀዳሚ የወደቀች አገር ስትባል፣ ዲሞክራቲክ ኮንጎ፣ ሱዳን፣  ደቡብ ሱዳን፣ ቻድ፣ የመን፣ አፍጋኒስታን፣ ሀይቲ ፣ ሴንትራል አፍሪካ ፣ ዝምባብዌ፣ ኢራቅ ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ፓኪስታን፣ ጊኒ፣ ጊኒ ቢሳው፣ ኬንያ፣ ኒጀር፣ ኢትዮጵያና ቡሩንዲ ተከታታዮችን ደረጃዎች ይዘዋል።
ከሀያዎቹ አገራት የተሻሉ ተብለው በሁለተኛው ምድብ ውስጥ ከሚገኙት መካከል ደግሞ ሶሪያ፣ ዩጋንዳ፣ ላይቤሪያ፣ ሰሜን ኮሪያ፣ ኤርትራ፣ ማይናማር፣ ካሜሩን፣ ስሪ ላንካ፣ ባንግሊያዲሽ፣ ኔፓል፣ ሞሪታኒያ፣ ኢስት ቲሞር፣ ሴራ ሊዮን፣ ግብጽ ፣ ቡርኪና ፋሶ፣ ኮንጎ፣ ኢራን፣ ማሊ፣ ርዋንዳ እና  ማላዊ ተመድበዋል።

ፕሬዚዳንት ግርማ ለፍትሕ ሚኒስቴር ያቀረቡት ጥያቄ ውድቅ ተደረገ

ሰኔ ፲፯ (አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና :-በከባድ የማታለል ወንጀል ተጠርጥረው ክስ የተመሠረተባቸው የጥንታዊት ኢትዮጵያ አርበኞች ማኅበር ፕሬዚዳንት፣ ዋና ጸሐፊና የአስተዳደርና ጠቅላላ አገልግሎት ኃላፊ፣ የተከሰሱበት ክስ እንዲቋረጥላቸው ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ፣ ለፍትሕ ሚኒስቴር የጻፉት ደብዳቤ ውድቅ መደረጉን  ሪፖርተር ዘገበ፡፡
ጋዜጣው ምንጮቹን ጠቅሶ እንደዘገበው ፤የአርበኞች ማኅበር ፕሬዚዳንት ሊቀ ትጉሃን አስታጥቄ አባተ ለፕሬዚዳንት ግርማ በጻፉላቸው የመማፀኛ ደብዳቤ መነሻነት ፤ፕሬዚዳንት ግርማ – ክሱ እንዲቋረጥላቸው ወይም በይቅርታ እንዲታለፉ  ደብዳቤውን የጻፉት በፍትሕ ሚኒስቴር የሕግና አስተዳደር ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ ለአቶ ብርሃኑ ፀጋዬ  ነው።
በከባድ የማታለል ወንጀል ተጠርጥረው በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ስምንተኛ ወንጀል ችሎት ክስ የተመሰረተባቸው፦ የኢትዮጵያ አርበኞች ማኅበር ፕሬዚዳንት ሊቀ ትጉሃን አስታጥቄ አባተ፣ ዋና ጸሐፊው ፲ አለቃ ሰጥአርጌ አያሌውና የአስተዳደርና ጠቅላላ አገልግሎት ኃላፊ አቶ በቀለ ሻረው ናቸው፡፡
ፕሬዚዳንት ግርማ በደብዳቤያቸው፦ ተጠርጣሪዎቹ በአገራቸው የጀግንነት ታሪክ ከፍተኛ ቦታ እንዳላቸው፣ ለአገር ልማትም በአሁኑ ጊዜ ከፍተኛ እገዛ እያደረጉ መሆናቸውንና ዕድሜያቸውም የገፋ መሆኑን በመግለጽ፣ መንግሥት ይቅርታ አድርጐላቸው ክሳቸው እንዲቋረጥ ነው የጠየቁት።

የኃይል መቋረጥ እያሰከተለ ያለው ቀውስ

June 24, 2013

ተሻለ መንግሥቱ (teshalem1@gmail.com)
ይህን ጦማር የምጽፈው፣ እንደልዩ ዕድል ወይም አጋጣሚ ሆኖ ከንፍሮ ውስጥ ጥሬ እንደሚገኝ ሁሉ በወያኔ መንደር ውስጥ ስለሀገራቸው የሚጨነቁ በጣት የሚቆጠሩ ባለሥልጣናትና የሥራ ኃላፊዎች ቢኖሩ “ሕዝቦቻቸው” በምን ዓይነት ችግር ውስጥ እንደሚገኙ ተረድተው ችግሩን ለመቅረፍ የተቻላቸውን ሁሉ እንዲያደርጉ ለመማጸን ነው፡፡ የገባንበት የችግር አዘቅት ተነግሮ የማያልቅ ቢሆንም በኤሌክትሪክ ኃይል ረገድ እየደረሰብን ያለው ጭቆናም ልበለው ረገጣ እጅግ የሚዘገንን ነው፡፡ እርግጥ ነው – ይህ ችግር የ‹ቅንጦተኞቹ› የከተማ ነዋሪዎችና መብራትና የኮረንቲ ኃይል በወሳኝነት ደረጃ ለሚያስፈልገን ዜጎች እንጂ አብዛኛውና ሌላውማ ዛሬ የሚቀምሳትን እንጂ የሚበራለትን መሻት ካቆመ ቆይቷል፡፡ ክትክታና ችቦም ቢሆን እያበራ የሚቀምሳት ቁራሽ እንጀራ ቢያገኝ – ያ ነው የጊዜው አንገብጋቢ ፍላጎቱ፡፡ ለብዙው ዜጋ የሚላስ የሚቀመስ ነገር ማግኘት ነው፡፡ ዱሮ በ‹ክፉው› ዘመን ኩንታል በቆሎ ከአምስት ብር በታች በሆነ ዋጋ እንዳልተሸመተ ዛሬ በ‹ፀሐዩ› የወያኔ ‹ደግ› ዘመን አንዲት የተጠበሰች በቆሎ በአምስት ብር ተገዝታ ወስፋት የሚሸነገልባት ሀገር ተፈጥራለች፡፡
“በሃያ ምናምን ዓመታት ውስጥ አንድ መንግሥት ከዚህም በላይ ሊሠራ ይችል ነበር፤ በዚህን ጊዜ ውስጥ ቢያንስ ረሀብን ማስወገድና ዴሞክራሲን ማስፈን ይቻል ነበር፤ ቅድሚያ ይህና ያ ቢሠራ ይበጅ ነበር፤…” የሚሉት ምናልባትም በተገቢነት ሊወሰዱ የሚችሉ አስተያየቶች እንደተጠበቁ ሆነው ባለፉት ሁለት አሠርት የወያኔ አገዛዝ ውስጥ በሀገራችን የታዩ የዕድገት ምልክቶች በቀላል የሚታዩ እንዳልሆኑ አፍ ቢክድ ኅሊና አይክድም፡፡ መከናወን ከሚገባው ይልቅ መሠራት የማይገባው እጅግ ብዙ መጥፎ ነገር በመታየቱ እንጂ ለተራበ አንጀት ብዙም ፋይዳ የማይሠጡ ለታይታዊ የዕድገት ፈለግ ግን የማይናቅ እመርታን የፈነጠቁ በርካታ የመንገድና የታህታይ መዋቅር  ግንባታዎች ተካሂደዋል፡፡ ይህን መመስከር ግን የወያኔን ዘረኛነትና በተለይም አንድን የሕዝብ አካል በሌሎች በማስጠላትና በግልጽም ሆነ በሥውር በማሰጨፍጨፍ ረገድ የተፈጸመውንና እየተፈጸመ ያለውን ታሪክ ይቅር የማይለው ደባ መካድ ማለት እንዳልሆነ መታወቅ ይኖርበታል፡፡ ለዚህ ነው ወያኔ ምንም ቢሠራ እጁ ዐመድ አፋሽ እንደሆነ ወደማይቀርለት የታሪክ ጉድጓድ ከመውረድ የማይድነው፤ ለዚህ ነው ወያኔ ከነዘረኛና ከፋፋይ ማፊያዊ ሥርዓቱ ከመንኮታኮት የማይተርፈው፡፡ በመግቢያነት ይህችን ያህል ከተነፈስኩ ወደርዕሴ ልግባ፡፡

“አሜሪካ አቋማን የምትፈትሽበት ወቅት ላይ ናት” ክሪስ ስሚዝ

"አሸባሪነትን መዋጋት የግፍ ማከናወኛ ሽፋን አይሆንም"

gear 1


ኢህአዴግ ሽብርተኝነትን በመዋጋት ስም ከአሜሪካ ጋር የመሰረተውን ግንኙነት አስታክኮ የሚፈጽመው ኢሰብዓዊ ድርጊት ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት የሌለው እንደሆነ ተገለጸ። አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የምትከተለውን ፖሊሲ የምትመረምርበት ወቅት ላይ ትገኛለች ተባለ። ኢህአዴግ ጸረሽብርተኝነትን ለአፈናና ለበጀት ማሟያ እየተጠቀመበት እንደማይቀጥል ተመለከተ።
አሜሪካና ሌሎች ለሰብአዊ መብት መከበር ዋጋ የሚሰጡ አገሮች በሙሉ በ”አዲስ አበባው” አገዛዝ ላይ ጠንካራ አቋም መያዛቸውን ያለ አንዳች ማወላወል ማሳየት እንደሚገባቸው እንደራሴ (ኮንግረስማን) ክሪስ ስሚዝ ያስታወቁት ሽብርተኛነትን አስመልክቶ ጠንካራ ማሳሰቢያ በማስቀመጥ ነው።
እንደራሴ ስሚዝ የኢትዮጵያ ጉዳይ የተደመጠበትን የምክክር ሸንጎ ከዘጉ በኋላ በተለይ ለጀርመን ድምጽ ሬዲዮ በሰጡት ቃለ ምልልስ እንደተናገሩት “አሜሪካ በኢህአዴግ ላይ ያላትን አቋም የምትመረምርበት ወቅት ላይ ትገኛለች” ብለዋል።
አሜሪካ ከሰብአዊ ርዳታ ጋር በተያያዘ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደምታደርግና በተለይም ኢትዮጵያና አሜሪካ አሸባሪነትን በመዋጋት በኩል አብረው እንደሚሰሩ ያመለከቱት እንደራሴው፣ “ሽብርንና ሽብርተኛነትን የመታገል ትብብር ግን የዜጎችን ሰብአዊ መብት ለመርገጥ ፍቃድ ማግኛ አይደለም። የመብት ረገጣ ሽፋን ሊሆን አይገባም” በማለት የኢህአዴግና የመሪዎቹን ተግባር ኮንነዋል።

Sunday 23 June 2013

በአቃቤ ሕግና በፍረድ ቤቱ መካከል አለመስማማት እየነገሰ መሆኑ ተሰማ!

June 23, 2013

ቅዳሜ ሰኔ 15/2005
‹‹ዳኞቹ እናንተ ናችሁ እኛ?›› ከዳኞቹ መካከል አንዱ ለአቃቤ ሕጎቹ ከተናገረው!
የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት የክስ ሂደትን ታክኮ በአቃቤ ሕግና በዳኞች መካከል አለመስማማት መፈጠሩ ተነገረ፡፡ አለመስማማቱ የተፈጠረው አቃቤ ሕግ ለተደጋጋሚ ጊዜ በችሎት ውስጥ ከዳኞች ጭምር የበላይ መሆኑን ለማሳየት ጥረት በማድረጉ ነው ተብሏል፡፡ በዚሁ እያገባደድነው ባለው ሳምንት ተሰይሞ ምንም ሳያከናውን ተበትኖ በነበረው ችሎት ላይ አቃቤ ሕግ ቀድሞ ለፍርድ ቤት ሪጂስትራ ገቢ ማድረግ የነበረበትን ሲዲ እዚያው ለችሎቱ ገቢ ለማድረግ መሞከሩና ሲዲውን ገቢ ማድረግ የነበረበት ክሱ በተመሰረተበት ወቅት ማለትም (ከስድስት ወራት በፊት) ሆኖ ሳለ እስከአሁን ሳያስገባ መቆየቱ በዳኞቹና አቃቤ ሕጎቹ መካከል ፍጥጫ ጭምር እንዲፈጠር ምክንያት ሆኗል፡፡Ethiopian Musilms
ባለፉት ስድስት ወራት በነበሩት የችሎት ትእይንቶች በዳኞችና በአቃቤ ሕጎች ግንኙነት እንዲሁም የዳኞችን ሚና በመጫወት ላይ የሚገኙት አቃቤ ሕጎች መሆናቸውንና ይህም ምንም አይነት ፍትሀዊ አያያዝም ሆነ ፍርድ ከፍረድ ቤቱ ልንጠብቅ እንደማንችል በምንሰራቸው የችሎት ዘገባዎች ስንገልጽ መቆየታችን የሚታወስ ሲሆን አሁንም ይህ የአቃቤያን ሕጎች ከማንም በላይ ሆኖ በችሎት ለመታየት የሚያደርጉት ጥረት ዳኞችን ብስጭት ውስጥ ከትቶ ጠንካራ ቃላት እንዲሰነዝሩ ምክንያት ሆኗል፡፡ እንደ ፍረድ ቤት ምንጮች ዘገባ በእለቱ ችሎት መጀመር የነበረበት ከማለዳ 2፡30 ቢሆንም ዳኞች ፍረድ ቤት የደረሱት ከረፋዱ 4 ሰዐት ነበር ሆኖም አቃቤ ሕጎች ከዳኞች ጭምር በአንድ ሰዓት በመዘግየት ከቀኑ አምስት ሰአት መድረሳቸው የውዝግብ መነሻ ሊሆን ችሏል፡፡ ይህን መነሻ በማድረግም አንዱ ዳኛ ‹‹ዳኞቹ እናንተ ናችሁ እኛ?›› የሚል ንግግር የሰነዘሩ ሲሆን አቃቤ ሕግ የበላይ ሆኖ ለመታየት የሚያደርገውን ጥረት እንዲያቆምም ጠይቀዋል፡፡

አንድነት የፀረ-ሽብር አዋጁን ለማሰረዝ የ1ሚ. ሰዎችን ፊርማ ያሰባስባል

Written by  tor

አንድነት የፀረ-ሽብር አዋጁን ለማሰረዝ የ1ሚ. ሰዎችን ፊርማ ያሰባስባል
ዶ/ር ነጋሶ የመጀመሪያው ፈራሚ ሆነዋል
“የአገሩን በሬ በአገሩ ሰርዶ እንጂ በውጭ ተቋማት መተማመንይቅር” - ዶ/ር ያዕቆብ ኃ/ማሪያም
አንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ (አንድነት) ከትላንት በስቲያ በይፋ የጀመረው ህዝባዊ ንቅናቄ የፀረ-ሽብር አዋጁን ማሰረዝ ዋነኛ አላማው እንደሆነ ገለፀ፡፡ ለዚህ ዓላማውም የአንድ ሚሊዮን ሰዎችን የድጋፍ ፊርማ (ፒቲሽን) በዕለቱ ማስፈረም የጀመረ ሲሆን የመጀመሪያው ፈራሚ የፓርቲው ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ሆነዋል፡፡ ፓርቲው የፀረ-ሽብር ህጉን ለማሰረዝ ከሚንቀሳቀስባቸው ምክንያቶች አንዱ ህገ-መንግስቱን በእጅጉ የሚጥስና የኢትዮጵያን ዜጐች በማጥቃት የሚጀምር በመሆኑ ነው ብሏል - የህዝባዊ ንቅናቄው ኮሚቴ በሠጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፡፡
ፓርቲው “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” በሚል መሪ ቃል የጀመረው የሶስት ወር ንቅናቄ የአንድ ሚሊዮን ህዝቦችን ድምፅ በማሰባሠብ የአገሪቱን ዜጐችና ተቋማትን በማጥቃት፣ በሀይማኖት ጣልቃ በመግባት፣ ከአባትና እናት የተወረሠን ንብረትና ሀብት በሽብርተኝነት ስም የሚገፈውን አዋጅ ለማሰረዝ ጥረት እናደርጋለን፤ ወደ ክስም እንሄዳለን” ብሏል፡፡ “ይህ ማለት ግን ኢትዮጵያ ካላት ተፈጥሯዊ ሀብትና መሠል ጉዳዮች ጋር በተያያዘ የፀረ-ሽብር ህግ አያስፈልጋትም ማለት እንዳልሆነ የገለፁት የንቅናቄው ኮሚቴ አባል አቶ ትዕግስቱ አወል፤ አሁን ስራ ላይ ያለው የፀረ ሽብር አዋጅ ግን ሰዎችን እና ተቋማትን የሚያጠቃ ነው ብለዋል፡፡

Saturday 22 June 2013

የትኛው አማራጭ ለአሜሪካ?

“ኢህአዴግን ምን እናድርገው? ንገሩን!”

hearing3


አሜሪካ ከመቼውም ጊዜ በላይ ደንግጣለች። ኦባንግ እንዳሉት ለህዝባቸው “ሬት” ለምዕራባውያንና “ማር” (የቤት ቀጋ፤ የውጭ አልጋ) የነበሩት አምባገነን በድንገት እንደ ተነቀለ ቡሽ ተስፈንጥረው ከሲስተም መውጣታቸው አሜሪካንን አስጨንቋታል። በተለይም እሳቸው አፍነው የያዙት የስርዓቱ “ክፉ ጠረን” አሁን እነርሱ (አሜሪካውያኑ) ደጅ የደረሰ ያህል መፍትሄ ለመፈለግ የወሰኑ ይመስላሉ። አውቀውና ፈቅደው ሲታለሉ የቆዩበትን ጊዜ አስልተው መንገዳቸውን የማስተካከል ስራ የጀመሩት ዛሬ አይደለም። አንዳንድ ምንጮች እንደሚሉት ከመለስ ሞት በኋላ አሜሪካ በምስራቅ አፍሪካ ላይ ሚዛኗን ሊያስታት የሚችል ውድቀት የሚደርስባት ኢትዮጵያ ላይ ያላትን አቋም ማስተካከል ሲያቅታት ብቻ እንደሆነ ይናገራሉ።
“… ሆን ተብሎ በተቀነባበረ እቅድ ህወሃት አዲስ አበባን እንዲቆጣጠር የተወሰነው ውሳኔ አሳዛኝና ከቶውንም ሊታመን የማይችል ነው። የሰከረ ርዕዮት ዓለም የሚከተሉ፣ በብሄርና በጎሳ ፖለቲካ ላይ የተተከሉ ጠባብ ቡድኖች፣ በስታሊናዊ መርህ የተጠመቁ፣ እንኳንስ 50 ሚሊዮን ህዝብ ያላት አገር ቤተሰብን የመምራትና የማስተዳደር ተሞክሮ የሌላቸው፣ አገርን መምራትን የሚያክል ታላቅ ሃላፊነት ማሸከም ለኔ ከአእምሮ በላይ ነው …” የዛሬ 22ዓመት ኮሎኔል ጎሹ ወልዴ ከተናገሩት፡፡

Friday 21 June 2013

“Ethiopia After Meles: The Future of Democracy and Human Rights”

Obang O. Metho's Testimony

obang at hearing


Testimony before the Subcommittee on Africa, Global Health, Global Human Rights and International Organizations
Date:
June 20, 2013
Given by:
Mr. Obang O. Metho, Executive Director
Solidarity Movement for a New Ethiopia
 “Ethiopia After Meles:
The Future of Democracy and Human Rights”
I would like to thank the Chairman of the Committee on Foreign Affairs, Congressman Edward Royce, and all ranking members of the Subcommittee on Africa, Global Health, Global Human Rights and International Organizations for this important opportunity to examine the Ethiopian Government’s observance of democratic and human rights principles in post-Meles Ethiopia.

Tuesday 18 June 2013

የሙስና ምርመራ እየተወሳሰበ ነው!

"መበላላት እንዳይጀመር ስጋት አለ"

sheraton


በጉምሩክና ገቢዎች ባለስልጣን የተጀመረው የጸረ ሙስና ዘመቻ ተከትሎ እየተካሄደ ያለው ምርመራ እየተወሳሰበ መሔዱ ተሰማ። በከፍተኛ የሙስና ወንጀል የተጠረጠሩ ተከሳሾች የሚሰጡት መረጃ መበላላት ያስነሳል የሚል ፍርሃቻ እያስነሳ ነው። “ሰፈር የለየው” የጸረ ሙስና ዘመቻ የፈጠረው ስጋት የሃይል ሚዛን የያዙትንም ስጋት ውስጥ ከትቷል።
በኢትዮጵያ ባለፉት 10 ዓመታት ውስጥ የታየው የውስን ሰዎች በድንገት በመበልጸግ ከባለስልጣኖችና ከከፍተኛ የስርዓቱ ሰዎች ቤተሰቦች ጋር በሚከናወን መተሳሰር አማካይነት እንደሆነ ከህዝብ የተሰወረ አይደለም። ሰሞኑንን ይፋ የተደረገው የባንክና የንብረት እግድ እንዳመለከተው የዝርፊያው ሰንሰለት በቤተሰብ የታጠረ መሆኑን ነው።
አቶ መለስ ከድነው ያቆዩትና የሳቸውን ሞት ተከትሎ ከፖለቲካው ልዩነት ጋር በተያያዘ እንደተጀመረ የሚነገርለት የጸረ ሙስና ዘመቻ፣ በመንግስት በኩል “ቆራጥ” አቋም የተያዘበት እንደሆነ ቢነገርም አስጊ ሁኔታ እየተፈጠረ ስለመሆኑ የጎልጉል የጸረ ሙስና ኮሚሽን ምንጮች ይናገራሉ።

Monday 17 June 2013

የቢሮ ኃላፊው በሙስና ላይ ምስክር ሳይሆኑ ተገደሉ

“ብዙ ሳይታወቅ የተገደሉ ተስፋዬዎች አሉ”

food


በነበራቸው የስራ ሃላፊነት በድብቅ መረጃ ሲያሰባስቡ ቆይተው ለመንግስት ካጋለጡ በኋላ ራሳቸውን ደብቀው የነበሩት አቶ ተስፋዬ ኢሬሣ ምሳ እየተመገቡ ህይወታቸው ማለፉ ተሰማ። አቶ ተስፋዬ ሰኞ ለጸረ ሙስና ኮሚሽን የምስክርነት ቃላቸውን ለመስጠት ከኮሚሽነር አሊ ሱሌማን ጋር ቀጠሮ ይዘው ነበር።
በቅርቡ ወደ ፌደራል መንግስት የተዛወሩት የጋምቤላ የቀድሞ ፕሬዚዳንት የነበሩት አቶ ኡሞት ኦባንግ፣ ከ83 ሚሊዮን ብር በላይ አላግባብ ለግል ጥቅማቸው ማዋላቸውን፣ እንዲሁም በክልሉ የሚፈጸሙትን የተጭበረበሩ የበጀት አፈጻጸሞችንና ምዝበራዎችን የሚያጋልጡ ሰነዶችን በሚስጥር በማደራጀት ለኢህአዴግ ያቀረቡት አቶ ተስፋዬ አሟሟታቸው አነጋጋሪ ሆኗል።
አቶ ተስፋዬ ኢሬሳ ከፍተኛ ምስጢር ያላቸውን ሰነዶች በመያዝ ከመታሰራቸው በፊት መሰወራቸውን፤ “የቢሮ ሃላፊው ይዘው የተሰወሩት መረጃ አቶ ኦሞት የፈረሙባቸው ከፍተኛ የገንዘብ ሰነዶችና ሙስና የተከናወነባቸው የኮንስትራክሽንና የተለያዩ መረጃዎች ናቸው። መረጃዎቹ አንድ ቀን ህዝብ ፍርዱን ይሰጥ ዘንድ ይፋ ይሆናሉ” በሚል ጎልጉል ምንጮቹን ጠቅሶ በ (ጥቅምት 19፤2005/October 29, 2012) መዘገቡ ይታወሳል

Sunday 16 June 2013

ከፍተኛ የደህንነት ሹም ከስልጣን ተነሱ (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

June 16, 2013

ከኢየሩሳሌም አርአያ
የሕወሐት አባልና የአገር ውስጥ ደህንነት ዋና ሃላፊ አቶ ወልደስላሴ ከስልጣናቸው እንዲነሱ መደረጉን የቅርብ ምንጮች አስታወቁ። ወ/ስላሴ ከስልጣን እንዲነሱ ያደረጉት የደህንነት ዋና ሹም አቶ ጌታቸው አሰፋ መሆናቸውን ምንጮቹ ጠቁመዋል። የሁለቱ ሹማምንት ፀብ ውስጥ ለውስጥ ሲብላላ ቆይቶ መጨረሻ መፈንዳቱ ታውቋል። በመቀሌ በተካሄደው የፓርቲው ጉባኤ አቶ ጌታቸው የፓርቲው ማ/ኮሚቴ አባል ሆነው እንዳይመረጡ ሰፊ ቅስቀሳ ሲካሂድ የቆየው ወ/ስላሴ በመጨረሻም የአባላት ምርጫ ሲካሄድ ባቀረበው ተቃውሞ ላይ «..ጌታቸው የተሰጠውን የፓርቲና መንግስታዊ ሃላፊነት በአግባቡ እየተወጣ አይደለም፤ የአልሙዲ ተላላኪና አሽከር ሆኗል… የአላሙዲ አገልጋይ ሆኖዋል… ስለዚህም በማ/ኮሚቴ አባልነት መካተት የለበትም..» ሲል መናገሩን ያወሱት ምንጮቹ፣ የወ/ስላሴ ተቃውሞ ተቀባይነት ባለማግኘቱ አቶ ጌታቸው በማ/ኮሚቴ አባልነታቸው እንዲቀጥሉ መደረጉን አያይዘው ገልፀዋል።…
አቶ ጌታቸው በቅርቡ በወሰዱት የአፀፋ እርምጃ ወ/ስላሴ ከአገር ውስጥ ደህንነት ሃላፊነታቸው እንዲነሱ በማድረግ እንደተበቀሏቸው ማወቅ ተችሏል። በጎንደር ተወልደው ያደጉትና በሰባዎቹ መጀመሪያ አመታት ሕወሐትን የተቀላቀሉት አቶ ጌታቸው በአብዛኛው አመራር « ጥሩ ሰው ነው፣ ላመነበት ነገር ወደኋላ የማያፈገፍግ..» ተብሎ እንደሚነገርላቸው ምንጮቹ ጠቁመዋል።

Saturday 15 June 2013

Civil Servants in Oromia Forced to Become Members of the OPDO

Firehiwot Guluma Tezera | June 15, 2013

Firehiwot Guluma Tezera
Firehiwot Guluma Tezera
TPLF is forcing Oromo civil servants to become member of the Oromo Peoples’ Democratic Organization (OPDO). The Oromo civil servants are now facing a choice between becoming member of the organization they hate to be associated with, and immerse their hands into the dirty work of OPDO, which is arresting, torturing, and killing innocent Oromo’s, or lose their jobs. Living under difficult economic situation, job loss is a very serious matter which is considered a suicide in the Empire, and, therefore, the Oromo civil servants will have to think twice before saying “no” to the warning of the Wayyaanee authorities and endangering their life and their families.
Contrary to its “democratic” naming, the so called OPDO is an undemocratic “organization” created by the Tigrai Peoples’ Liberation Front (TPLF), from the war prisoners of the former military junta, Mengistu Haile Mariam in the jungles of Tigrai. It is a pseudo organization completely controlled by ruling party, the TPLF. The TPLF regime uses this organization to arrest, harass, torture, and kill innocent Oromo’s who do not support their tyrannical rule. Moreover, the OPDO is used by the TPLF leaders as a tool to abuse their political power and exploit the entire economy of Oromia for their personal account and build their home base of Tigrai regional state.

አገር በቤተሰብ ስትዘረፍ ኢህአዴግ የት ነበር?

“አዲስ አበባ የተገተሩት ህንጻዎችስ?”

የሁለት አገር ነዋሪዎች


በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉት ባለስልጣናት፣ ባለሃብት፣ ደላሎችና ባለድርጅቶች በልጆቻቸውና በቤተሰቦቻቸው ስም “ዘርፈው አስቀመጡት” የተባለው ንብረታቸውና የባንክ ሂሳባቸው መታገዱ ታወቀ። የዜናውን ይፋ መሆን ተከትሎ አዲስ አበባን ያጥለቀለቋት ህንጻዎችና የንግድ ድርጅቶች ጉዳይ ለምን ዝም ተባሉ የሚል ጥያቄ እየተሰነዘረ ነው።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት የነበሩት አቶ ነጋ ገብረ እግዚአብሔር 54 ተሽከርካሪዎች ተይዘውባቸዋል። ገንዘቡን ሳይጨምር 54 ተሽከርካሪዎች በስማቸው ተመዝግበው የተያዙባቸው አቶ ነጋ ፣ የወ/ሮ አዜብ መስፍን የንግድ ሽሪክ እንደሆኑ የሚያውቋቸው ይገልጻሉ። በኢህአዴግ ጉባኤዎች ላይ የማይቀሩት አቶ ነጋ በየስብሰባው ወቅት ሻይና ቡና ሲሉ ከወ/ሮ አዜብ ጋር አብረው እንደሆነ የሚገልጹት ታዛቢዎች፣ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን “አትሌት ናቸው” በሚል ወደ ውጪ በጉቦ የላካቸው ሰዎች ጉዳይም ከሳቸው ጋር እንደሚያያዝ ይጠቁማሉ።  ከጨው ንግድ፣ ከካሜራ ፊልም ብቸኛ አስመጪነት ሌላ በአሁኑ ወቅት ሂልተን ጀርባ፣ አዲስ አበባ ስታዲየም ቪክ ሬስቶራንት ጎን ግዙፍ ህንጻ ያስገነቡት አቶ ነጋ ቃሊቲ ባላቸው የነዳጅ ማደያ የከፈቱት ብቸኛ የክብደት መለኪያ/የከባድ የጭነት መኪኖች የክብደት መለኪያ “የገንዘብ ማምረቻ ማሽን” አግባብነት የሌለው ቢዝነስ እንደሆነ ቅሬታ ሲቀርብበት የቆየ የግል የንግድ ተቋማቸው ነው። ቀደም ሲል ከኤርትራዊያን ጋር አብረው ሲሰሩ የነበሩት አቶ ነጋ ሃብታቸው በድንገት የተመነጠቀው ከ1991 ኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ጀምሮ እንደሆነ የሚያውቋቸው ይናገራሉ።

Thursday 13 June 2013

HRLHA Participates in 23rd Regular Session of UN Human Rights Council

HRLHA | June 12, 2013

HRLHA FinegeneavaThe Human Rights League of the Horn of Africa (HRLHA) has participated in the 23rd regular session of the UN Human Rights Council held at the UN Geneva Headquarters in Switzerland from May 27 to June 14, 2013. The event particularly hosted by the HRLHA on the past and present human rights situations in Ethiopia took place on the 6th of June, 2013.
HRLHA was represented, at the 23rd regular session, by Mr. Garoma B. Wakessa, the Executive Director of HRLHA and Mr. Tesfaye Deressa, Chief Investigator; and the representatives of HRLHA did presentations on the Adverse Roll of land grab and the encroachments of fundamental rights in Ethiopia respectively. In his presentation under the title “The Consequences of Land Grab in Ethiopia”, Mr. Garoma elaborated on how local farmers in various parts of the country, in Oromia, Gambella and Benshangul regional states in particular, were evicted from their lands and livelihoods without consent and compensations, and ended up in joblessness and poverty. He has also pointed at how the Ethiopian Government has violated the international laws and instruments that relate to investments and/or developments through partnerships of Transnational Corporations and local governments.

Tuesday 11 June 2013

ኢትዮጵያና ግብጽ የቃላት ጦርነት ጀምረዋል

ሰኔ ፬ (አራት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-በሁለቱ አገሮች መካከል መተነኳኮሱ እየባሰ የመጣው  ዘንድሮ ግንቦት 20 ቀን የተከበረውን የገዥውን ፓርቲ በኣል  ምክንያት በማድረግ ኢትዮጵያ ፦” የ አባይ ወንዝን የተፋሰስ አቅጣጫ አስቀየስኩ” ብላ ማወጇን ተከትሎ ነው።
ይህን ተከትሎ በተለይ የግብጽ መንግስት -ከተቃዋሚዎቹ ጋር በመሆን በኢትዮጵያ ላይ እስከ ወታደራዊ ጥቃት ድረስ የሚደርስ እርምጃ ለመውሰድ የመከሩበት ስብሰባ በይፋ ታየ፤
ይሁንና የግብጽ መንግስት-ከተቃዋሚዎቹ ጋር  በመሆን ኢትዮጵያ ላይ ለመውሰድ ስለታሰበው እርምጃ  ሲመክሩበት የነበረው ስብሰባ በቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት መተላለፉ፤ግብጽ -ኢትዮጵያን ለማስፈራራት መፈለጓን የሚያሳይ ተራ ጨዋታ ነው በሚል ብዙዎች ትኩረት ሳይሰጡት ቆይተዋል
ይህ በ እንዲህ እንዳለ ትናንት  የግብጹ ፕሬዚዳንት መሀመድ ሙርሲ ፦ኢትዮጵያ በምትሠራው ግድብ ሳቢያ ወደ ግብጽ ከሚፈሰው የ አባይ ወንዝ የጠብታ ያህል ከቀነሰ አገራቸው ግብጽ ማናቸውንም እርምጃዎች ኢትዮጵያ ላይ ለመውሰድ ዝግጁነቱ እንዳላት አስታውቀዋል።
ከ ኢትዮጵያ ጋር ጦርነት እንደማይፈልጉ፤ ግድቡን ለማስቆም የሚያደርጉት ጥረት ካልተሳካ ግን ሁሉንም አማራጭ እርምጃዎች ለመውሰድ እንደሚገደዱ ነው ፕሬዚዳንቱ የተናገሩት።
ኢትዮጵያ – አቅጣጫውን የቀየረው የወንዙ ፍሰት ሀይል ካመነጨ በሁዋላ ተመልሶ በመደበኛው መስመር እንደሚፈስ እና  በግብጽም ሆነ በሱዳን ላይ የሚፈጥረው ነገር እንደማይኖር ደጋግማ ብታሳውቅም፤ፕሬዚዳንት ሙርሲ ፈጽሞ የግብጽ የውሀ ደህንነት ሊነካ አይገባም! በማለት የ ኢትዮጵያን ምላሽ እንደማይቀበሉት አስታውቀዋል።

Saturday 8 June 2013

Oromo refugees attacked in Egypt as the Nile crisis deepens

oromocairoBy Mohammed Ademo
(OPride) – An Oromo interpreter for UNHCR in Cairo was beaten, denied police services, and subsequently charged extra for medical care on Thursday in retaliation for Ethiopia’s diversion of the Nile River to build a $4.7 billion hydroelectric dam, according to locals.
“Our friend was beaten seriously by a group of Egyptian youth and he was nearly killed,” wrote Abdulkadir Noor Gumi, a Cairo-based community activist, in a frantic appeal letter sent to OPride.com. “He was beaten by chain, metal, and stick...he had a head injury and other injuries on his body.”
When Ethiopia began diverting the flow of the Nile on May 28 for its so-called Grand Ethiopian Renaissance Dam – the largest in Africa with a 6000 megawatts capacity, the Egyptian blogosphere and media exploded as many called for swift action. Immediately following the announcement, an angry mob gathered in front of the Ethiopian embassy in Cairo to denounce the move, according to media reports.

Friday 7 June 2013

ኦባንግ ለኃይለማርያም ግልጽ ደብዳቤ ላኩ

ለማሰር መጣድፍ እንደማያዋጣ አስጠነቀቁ

obang metho1


ባለፈው እሁድ በሰማያዊ ፓርቲ የተጠራውንና በሰላም የተጠናቀቀውን ሰላማዊ ሰልፍ በማስመልከት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ ለጠ/ሚ/ር ኃይለማርያም ደሳለኝ ግልጽ ደብዳቤ ላኩ፡፡ በደብዳቤው ላይ ኢህአዴግ ሰልፈኞቹንም ሆነ የፓርቲውን አመራሮች ለማሠር የሚያደርገውን ሃሳብ ከመፈጸም እንዲቆጠብ ማስጠንቀቂያ ልከዋል፡፡
አቶ ኦባንግ በደብዳቤያቸው ላይ በርካታ ጉዳዮችን የዳሰሱ ሲሆን በቅድሚያ ግን ጠ/ሚ/ር ኃይለማርያም ሠልፉን በመፍቀዳቸው ሊመሰገኑ እንደሚገባ ጠቅሰዋል፡፡ ይህንንም በማድረግ ከቀድሞው መሪ መለስ እንደሚለዩና ምናልባትም ህዝብን ለማዳመጥ ፍላጎት እንዳላቸው ጠቋሚ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ምክንያቱንም ሲያስረዱ መለስ በእንደዚህ ዓይነቱ ሠልፈኞች ላይ የህወሓት አልሞ ተኳሾች ተኩስ በመክፈት እንዲገደሉ ማድረገቸውና የፓርቲ አመራሮችን ማሳሰራቸውን እንደ ማስረጃ ጠቅሰዋል፡፡
የሕዝብ ጥያቄ በአግባቡ ምላሽ እስካላገኘ ድረስ እንዲህ ዓይነቱ የታቃውሞ ሠልፍ እየቀጠለ እንደሚሄድ የተናገሩት ኦባንግ የሕዝብን ጥያቄ ማዳመጥና ተገቢውን ምላሽ አማራጭ መፍትሔ የሌለው ጉዳይ እንደሆነ አመልክተዋል፡፡ ከዚህ ሌላ በአንዳንድ የኢህአዴግ አመራሮች ሠልፉ የጥቂቶች እንደሆነ ለማስመሰል የተወሰደው አካሄድ ፈጽሞ እንደማይሠራ ጠቁመዋል፡፡ በሠልፉ ላይ የታዩት ኢትዮጵያውያን ከሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል የተውጣጡ እንደሆኑና እነዚህም ክርስቲያን፣ ሙስሊም፣ የማያምኑ፣ ሴቶች፣ ወጣቶች፣ አረጋውያን፣ የመንግሥት ሠራተኞች፣ ሥራ የሌላቸው፣ አካለ ስንኩላን፣ የኢህአዴግ አባላት፣ ተማሪዎች፣ ወዘተ መሆናቸውን በማስረጃ አስረድተዋል፡፡

Thursday 6 June 2013

ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ (መንግስት ለሕዝብ ጥያቄዎች ምላሽ እንዲሰጥ አሁንም እንጠይቃለን!)

ሰማያዊ ፓርቲ

ሰማያዊ ፓርቲ የጠራው ታላቅ ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ ግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ.ም በርካታ ሕዝብ በተገኘበት ደማቅ ሆኖ ተካሂዷል፡፡ ለዚህ ሰልፍ መሳካት ከፍተኛ ድጋፍና አስተዋፅኦ ላደረጉ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማህበራት፣ የመገናኛ ብዙኃንና በሰልፉ ለተሳተፉ ዜጎች እንዲሁም ሰልፉ በሰላም እንዲጠናቀቅ ለረዱ የፀጥታ ኃይሎች ፓርቲያችን ልባዊ ምስጋናውን ያቀርባል፡፡Blue Party Ethiopia
ከዚህ በተቃራኒ ግን ይህንን ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ ተከትሎ የገዥው ፓርቲ ባለስልጣናትና የመንግስት ተወካዮች የተለመደውን ተልካሻ አስተያየቶች ሰጥተዋል፡፡ የገዥው ፓርቲ ተወካይ ሰልፉን አስመልክቶ በሰጡት አስተያየት “የሐይማኖት አክራሪነት አጀንዳው አድርጎ ሲንቀሳቀስ የነበረው ሰማያዊ ፓርቲ ዛሬ በጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ድብቅ አጀንዳው ገሃድ ወጣ” በማለት በሰጡት አስተያየት ፓርቲውን ለማንቋሸሽና ለማራከስ ሞክረዋል፡፡ ይህም ፓርቲውን በእጅጉ ያስቆጣ ነው፡፡ ይህ ዓይነቱ መሰረተ ቢስ ፍረጃ የገዥው ቡድን አባላት ለንግግራቸውና ለሚሰጡት አስተያየት ሚዛን የሌላቸው ከመሆኑ ውጭ በፓርቲው ፕሮግራምም ሆነ እንቅስቃሴ ከአሸባሪነት ጋር የሚያገናኘውን አንዳችም ነገር አልጠቀሱም፡፡ ፓርቲው በሕጋዊ መንገድ ተመዝግቦ እየተንቀሳቀሰ የሚገኝ እና በሕገ መንግስቱ በተሰጠው መብት ተጠቅሞ በሕጋዊ ሥነስርዓት ያደራጀውን ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ በእንዲህ አይነት መንገድ መፈረጅ ሰልፉ ከተጠራበት ዓላማና መንፈስ በእጅጉ የራቀ አስተያየት ሆኖ አግኝቶታል፡፡

ኢትዮጵያ ለግብፅ ማስጠንቀቂያ ሰጠች


EMF: በአባይ ግድብ የተነሳ በሁለቱ አገሮች መካከል ያለው ፍጥጫ ከዚህ በፊት ከነበረው ሁኔታ በተለየ መልኩ ውጥረት የነገሰ ይመስላል። በተለይም የግብፁ ፕሬዘዳንት “ቅንጣት ውሃ አናስነካም!” ከማለት አልፈው ካቢኔያቸውውን ሰብስበው ሲነጋገሩ በቀጥታ በቴሌቪዥን ሲተላለፍ፤ ኢትዮጵያን ለመምታት የተለያዩ ሃሳቦች ሲያቀርቡ ከታየ በኋላ፤ የግብፅ እና የኢትዮጵያ ጉዳይ የሰሞኑ መነጋገሪያ ሆኖ ቆይቷል። በተለይም ሰሜን ሱዳን እና ግብፅ የናይል ወንዝን አስመልክቶ የሁለትዮሽ ወታደራዊ ስምምነት ስላላቸው፤ ሱዳን ለግብፅ በመወገን… መንደርደሪያ ከሰጠቻት ግብፅ ከሳምንት በፊት የገዛቻቸውን ኤፍ 16 ጄቶች ልትጠቀም ትችላለች የሚል ስጋት አለ።
F 16 ተዋጊ ጄቶችን በመጠቀም ግብፅ በአለም 4ኛ ደረጃ ላይ የምትገኝ ሲሆን፤ ከዚህ ቀደም ከነበራት 240 ኤፍ-16 ተዋጊ ጄቶች በተጨማሪ ነው - 20 ጄቶችን የገዛችው። እንዲህ አይነት ጄቶች ደግሞ በፍጥነትም ሆነ ረዥም ርቀት በመሄድ እና በማናቸውም አቅጣጫና ማዕዘን መገለባበጥ የሚችሉ ናቸው።
F 16 ተዋጊ ጄቶችን በመጠቀም ግብፅ በአለም 4ኛ ደረጃ ላይ የምትገኝ ሲሆን፤ ከዚህ ቀደም ከነበራት 240 ኤፍ-16 ተዋጊ ጄቶች በተጨማሪ ነው – 20 ጄቶችን የገዛችው። እንዲህ አይነት ጄቶች ደግሞ በፍጥነትም ሆነ ረዥም ርቀት በመሄድ እና በማናቸውም አቅጣጫና ማዕዘን መገለባበጥ የሚችሉ ናቸው።
F 16 ተዋጊ ጄቶችን በመጠቀም ግብፅ በአለም 4ኛ ደረጃ ላይ የምትገኝ ሲሆን፤ ከዚህ ቀደም ከነበራት 240 ኤፍ-16 ተዋጊ ጄቶች በተጨማሪ ነው – 20 ጄቶችን የገዛችው። እንዲህ አይነት ጄቶች ደግሞ በፍጥነትም ሆነ ረዥም ርቀት በመሄድ እና በማናቸውም አቅጣጫና ማዕዘን መገለባበጥ የሚችሉ ናቸው።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ኢትዮጵያ ለግብፅ የማስጠንቀቂያ መልዕክት ከመላክ አልፋ፤ በኢትዮጵያ የሚገኘው የግብፅ አምባሳደር በኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር መስሪያ ቤት ተገኝቶ የአገሩን የግብፅን አቋም እንዲያስረዳ ጥብቅ ማሳሰቢያ ተልኮለታል። እንግዲህ አምባሳደሩ የውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ የሰጣቸውን ማሳሰቢያ ተቀብለው ቃላቸውን ይሰጣሉ ወይስ ጥሪውን ንቀው ይተዉታል?  የአምባሳደሩ ምላሽ ብዙ ነገር ሊለውጥ ይችላልና መጨረሻውን  አብረን እንከታተላለን።

Wednesday 5 June 2013

“ይህ መንግሥት አይመጥነንም”

የ“ምርቃና” መግለጫ ለኢህአዴግ ድንጋጤ

shemelis2-


ሰሞኑን ኢትዮጵያ የዓለም መገናኛ አጀንዳ ሆናለች። ለዘመናት እጇን ኢትዮጵያ ላይ ተክላ የኖረችው ግብጽ የምትዝተው ዛቻና፣ በቅርቡ ተቋቁሞ ታላቅ ታሪክ በማስመዝገቡ የተረጋገጠለት ሰማያዊ ፓርቲ ያዘጋጀው ሰላማዊ ሰልፍ አጀንዳዎቹ ናቸው።
በወጣት አመራሮች የተገነባውና በርካታ ሴት አባላት እንዳሉት የሚነገርለት ሰማያዊ ፓርቲ በጠራው ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ በዋናነት የተገኘው ድል የፍርሃት ደመና መገፈፉ ነው። አቶ መለስ ባስተላለፉት ትዕዛዝ በ1997 ዓ.ም ዜጎች አልመው በሚተኩሱ የአጋዚና ታማኝ የህወሃት አባሎች ደረትና አናታቸው እየተወጋ እንዲገደሉ ከተደረገ በኋላ የተቃውሞ ሰልፍ የማይታሰብ ሆኖ ላላፉት ስምንት ዓመታት ቆይቶ ነበር።
ከዳር እስከዳር ድምጽ አልባ ሆኖ የተሸነፈው ኢህአዴግ በጠመንጃ ፣ በወቅቱ የነበሩት የቅንጅት አመራሮች ታሪካዊና ሊረሳ የማይችል ስህተት ተዳምረው የህዝቡን ቅስም የሰበረው የ1997 ዓ ም ምርጫ ጣጣውና ቆፈኑ እንዲሁ በቀላሉ የሚለቅ እንዳልሆነ በወቅቱ አስተያየት ተሰጥቶ ነበር።

በጦርነቱ ሰበብ በተዘረፈ ሐብት የሕወሃት ጄነራሎች ሚሊየነር ሆነዋል፡፡


“ማን ያውራ የነበረ…….ማን ያርዳ የቀበረ……”
“….የጦር መኮንን ሆነህ እንደባለሙያ ስታየው ውጊያው በጥቅሉ የሙያ ብቃት ያልታየበት አሳፋሪ ጦርነት ነበር ማለት ይቻላል፡፡በጃንሆይ እና በደርግ ዘመን ኤርትራ ላይ ውጊያ ተደርጎ የተሰዋው ዜጋችን ቁጥር ከ250 ሺ እስከ 300 ሺ ይደርሳል፡ከዚህ አንፃር ወያኔ በአንድ ዓመት ውስጥ ኤርትራ ላይ ያስፈጀው የወታደር ቁጥር በጣም አሳፋሪ ነው፡፡ከመከላከያ የሰው ኃይል አስተዳደርና ልማት መምሪያ ሰነዶች ያገኘሁት መረጃ እንደሚያሳየው በጠቅላላ በኢትዮ ኤርትራ ውጊያ 98,700 ወታደር ሲሞትብን 194¸300 ቁስለኛ ተረክበናል፡፡ ከኦርዲናንስ እዝ ያገኘሁት መረጃ ደግሞ መጀመሪያ ለውጊያ ከተዘጋጀው ከባድ መሳሪያ 2ሐ3ኛው መውደሙን ነግረውኛል፡፡ ይህንን ትርጉም አልባጦርነት የመሩት መሪዎች ሰዓረ መኮንን፣ ሳሞራ የኑስ፣ዮሀንስ ገብረመስቀል፣ታደሰ ወረደ፣ኳርተር /አብርሃ ወልደማርያም/፣ ብርሃነ ነጋሽ የተባሉት ጄነራሎች ናቸው፡፡
የጦርነቱ ማዕከላዊ እዝ አባላት ደግሞ መለስ ዜናዊ፣ ስዬ አብርሃ፣ ተወልደ ወልደማርያም፣ አለምሰገድ ገብረአምላክ፣ ተፈራ ዋልዋ፣ ፃድቃን ገብረትንሳኤ እና ክንፈ ገብረመድሕን ነበሩ፡፡ ያ ሁሉ ዜጋ ያለቀበትና ያ ሁሉ የሀገር ሀብት የወደመበት ጦርነት ከጦርነት አመራር ችግር መሆኑ በግልፅ እየታወቀ አንድም የጦርነቱ መሪ ተጠያቂ ሳይሆን እንዲሁ መቅረቱ በጣም ያሳዝናል፡፡…….”
ኮሎኔል አለበል አማረ
የአጋዚ ኮማንዶ አመራር አባል የነበሩ እና በግንቦት 7 መፈንቅለ መንግስት ሙከራ ተጠርጥረው ዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት የተፈረደባቸው
ሌላኛው ኮሎኔል ደግሞ እንዲህ ይሉናል፡

Tuesday 4 June 2013

Human rights situations that require UNHRC’s attention – Ethiopia

United Nations Human Rights Council

23rd Session, Geneva, Switzerland
HRLHA
HRLHA
June 4, 2013
Oral Statement: by Mr. Garoma Wakessa
Executive Director the Human Rights League of the Horn of Africa (HRLHA)
Item 4: Human rights situations that require the Council’s attention – Ethiopia
Thank You Mr. Chairman,
Human rights violations in Ethiopia are gross, are of all kinds and widespread. Due to the limited time allotted to this Oral Statement, I will focus on the most crucial components.
The current Ethiopian Government has continued systematic restrictions on basic rights and freedoms to which all humans are entitled, including freedom of thought and expression, and civil and political rights. The independent media, political opposition parties, and civil societies, are continuously harassed and intimidated by the government; many of them are outlawed, and political leaders are sentenced to long prison terms under the so- called Anti-Terrorism proclamation.
The provisions of Ethiopia’s 2009 Anti-Terrorism Proclamation define terrorist activities so vaguely that they are easily used to criminalize all civil society activists and political opposition leaders, supporters, and peaceful demonstration organizers.
Today, media practitioners in Ethiopia face charges such as treason and terrorism simply because they put information on paper -and publish it. Opposition political party leaders and supporters face the same charge because they exercise their political freedoms.

Monday 3 June 2013

ምርመራው ወደ አቃብያነህጉ ተዛወረ!

የሙስናው “ሻርኮች” በዒላማ ውስጥ?

berhane


* “አዲስ ነገር የለም” ጸረ ሙስና ኮሚሽን
በተለያዩ ከፍተኛ ወንጀሎች በተጠረጠሩ ሰዎች ላይ የተከፈቱ ክሶችን በማፈንና በመመሪያ ፍትህ በማዛባትና በማቋረጥ ወንጀል የተጠረጠሩ አቃቤያነህግ ላይ ምርመራ መጀመሩ ከፍተኛ ድንጋጤ መፍጠሩ ተሰማ። በተለይም ከወንጀል ጋር ቁርኝት እንዳላቸው በህዝብ የሚታወቁ ክፍሎች ክፉኛ መደናገጣቸው ተሰምቷል።
በሙስና የተጠረጠሩት የጉምሩክ ባለስልጣናት፣ ተባባሪ ነጋዴዎችና ደላሎች መታሰራቸውን ተከትሎ ከተፈጠረው ስሜት በላይ ከፍተኛ መደናገጥ የፈጠረው ዜና አዲስ አድማስ ጋዜጣ ቅዳሜ እለት ለንባብ ያበቃው ዜና ነው።
በቅርቡ ከሃላፊነታቸው የተነሱት የፍትህ ሚኒስትር አቶ ብርሀነ ሃይሉና ከአስር በላይ አቃብያነህግ በተለያዩ ጉዳዮች የተመሰረቱ ክሶች እንዲቋረጡ አድርገዋል በሚል ተጠርጥረው መመርመራቸው በትክክል ከተሰራበት ዋንኛ የሚባሉትን የሙስና ወንጀል “ሻርኮች” በቁጥጥር ስር ለማዋል እንደሚያስችል ከፖሊስ ያገኘነው ጥቆማ ያመለክታል።
“የበርካታ ጉዳዮች ክስ እንዲቋረጥ መደረጉን እናውቃለን” በማለት ለጎልጉል ጥቆማ የሰጡት የፖሊስ አባላት “ይህ ጉዳይ ከተነሳና በትክክል ከተሰራበት የማይጎተት የለም” በማለት በትዕዛዝና በመመሪያ የተቋረጡ የምርመራና የክስ ፋይሎች በርካታ መሆናቸውን ያስረዳሉ።
ተቋማትንና ጉዳዮችን ስም በመጥራት መናገር እንደሚቻል የጠቆሙት ክፍሎች እንዲቋረጡ  የተደረጉ የክስ ሂደቶችን አስመልክቶ ህዝብ ነጻ መድረክ ቢሰጠው የተሻለ እንደሆነ አመልክተዋል። የፌደራል የስነ ምግባርና የጸረ ሙስና ኮሚሽን የቅርብ ሰው የሆኑ የጎልጉል ምንጭ በበኩላቸው “ኮሚሽኑ የመረጃና የማስረጃ ችግር የለበትም። በርካታ አቤቱታዎች ቀርበውለታል። ግን ሳይፈቀድለት መራመድ አይችልም” በማለት ማነቆው ከላይ እንደሆነ አስረድተዋል።