የኦሮሚያ ተማሪዎች እያሰሙ ስላሉት ተቃውሞና በፀጥታ ኃይሎች ስለተወሰዱ እርምጃዎች የኢትዮጵያ ኤምባሲ ማብራሪያ ሰጥቷል፡፡
“የኦሮሞ ገበሬዎችን በዘዴ ማፈናቀልና ግድያን ጨምሮ በተማሪዎች ላይ እየተወሰደ ያለው የኃይል እርምጃ ይቁም” ሲሉ የጠየቁ የኦሮሞ ተወላጅ የሆኑ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያ አሜሪካዊያን ዛሬ ዋሽንግተን ዲ.ሲ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ የተቃውሞ ሰልፍ አካሂደዋል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ የኢትዮጵያ መንግሥት ፀጥታ ኃይሎች እየወሰዱ ያሉት የጭካኔ የኃይል እርምጃ ነው ሲል የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቹ ሂዩማን ራይትስ ዋች አስታውቋል፡፡
የዋሽንግተን ዲ.ሲ ሜትሮፓሊታን የኦሮሞ ወጣቶች ቡድን ያዘጋጀውና የመራው ሰልፍ ነው በኢትዮጵያ ኤምባሲ ደጅ ላይ የተካሄደው፡፡
ሰልፈኞቹ “ኢትዮጵያ ውስጥ የተቃውሞ ድምፃቸውን እያሰሙ ካሉ ተማሪዎች ጎን እንቀማለን፤ የኦሮሞ ገበሬዎችን ማፈናቀልን፣ መንግሥት እያከናወነ ባለው ሥራ ላይ ትኩረት ስለሳቡ ጥቃት በተሠነዘረባቸው ተማሪዎች ላይ የተፈፀመውን ጅምላ ግድያ እንቃወማለን” ብለዋል፡፡
የኦሮሞ ወጣቶች ቡድኑ ከሰልፉ ጋር አያይዞ ያወጣው የፕሬስ መግለጫ “ሥጋታችንን እያሰማን ነው፤ ኢትዮጵያ ውስጥ እየተፈፀመ ያለውን ልቅ የሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ረገጣ፤ በተለይ በውጤቱ በአሥር ሺሆች የሚቆጠሩ የኦሮሞ ገበሬዎችን ከአዲስ አበባ አካባቢ ሊያፈናቅል የሚችለውን የመንግሥት ዕቅድ በሰላማዊ መንገድ በተቃወሙ ተማሪዎች ላይ የተፈፀመውን ግድያ እየተከታተሉ እንዲዘግቡና እንዲያጋልጡ ለመገናኛ ብዙኃን ጥሪያችንን እናቀርባለን” ይላል፡፡
በኤምባሲው ደጅ ላይ የተካሄደውን በተመለከተ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ፐብሊክ ዲፕሎማሲና የኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊው አቶ ዋህደ በላይ በተፈጠረው ሁኔታ መንግሥት በእጅጉ ማዘኑን በይፋ መግለፁን ሕይወታቸው ለጠፋ ሰዎች ቤተሰቦችም ይህንኑ ማሳወቁን ገልፀዋል፡፡
“የኦሮሞ ገበሬዎችን በዘዴ ማፈናቀልና ግድያን ጨምሮ በተማሪዎች ላይ እየተወሰደ ያለው የኃይል እርምጃ ይቁም” ሲሉ የጠየቁ የኦሮሞ ተወላጅ የሆኑ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያ አሜሪካዊያን ዛሬ ዋሽንግተን ዲ.ሲ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ የተቃውሞ ሰልፍ አካሂደዋል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ የኢትዮጵያ መንግሥት ፀጥታ ኃይሎች እየወሰዱ ያሉት የጭካኔ የኃይል እርምጃ ነው ሲል የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቹ ሂዩማን ራይትስ ዋች አስታውቋል፡፡
የዋሽንግተን ዲ.ሲ ሜትሮፓሊታን የኦሮሞ ወጣቶች ቡድን ያዘጋጀውና የመራው ሰልፍ ነው በኢትዮጵያ ኤምባሲ ደጅ ላይ የተካሄደው፡፡
ሰልፈኞቹ “ኢትዮጵያ ውስጥ የተቃውሞ ድምፃቸውን እያሰሙ ካሉ ተማሪዎች ጎን እንቀማለን፤ የኦሮሞ ገበሬዎችን ማፈናቀልን፣ መንግሥት እያከናወነ ባለው ሥራ ላይ ትኩረት ስለሳቡ ጥቃት በተሠነዘረባቸው ተማሪዎች ላይ የተፈፀመውን ጅምላ ግድያ እንቃወማለን” ብለዋል፡፡
የኦሮሞ ወጣቶች ቡድኑ ከሰልፉ ጋር አያይዞ ያወጣው የፕሬስ መግለጫ “ሥጋታችንን እያሰማን ነው፤ ኢትዮጵያ ውስጥ እየተፈፀመ ያለውን ልቅ የሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ረገጣ፤ በተለይ በውጤቱ በአሥር ሺሆች የሚቆጠሩ የኦሮሞ ገበሬዎችን ከአዲስ አበባ አካባቢ ሊያፈናቅል የሚችለውን የመንግሥት ዕቅድ በሰላማዊ መንገድ በተቃወሙ ተማሪዎች ላይ የተፈፀመውን ግድያ እየተከታተሉ እንዲዘግቡና እንዲያጋልጡ ለመገናኛ ብዙኃን ጥሪያችንን እናቀርባለን” ይላል፡፡
በኤምባሲው ደጅ ላይ የተካሄደውን በተመለከተ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ፐብሊክ ዲፕሎማሲና የኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊው አቶ ዋህደ በላይ በተፈጠረው ሁኔታ መንግሥት በእጅጉ ማዘኑን በይፋ መግለፁን ሕይወታቸው ለጠፋ ሰዎች ቤተሰቦችም ይህንኑ ማሳወቁን ገልፀዋል፡፡