Wednesday, 7 May 2014

የኦሮሞ ተወላጆች ሰልፎች ዋሽንግተንና ለንደን ላይ ተካሄዱ


የኦሮሚያ ተማሪዎች እያሰሙ ስላሉት ተቃውሞና በፀጥታ ኃይሎች ስለተወሰዱ እርምጃዎች የኢትዮጵያ ኤምባሲ ማብራሪያ ሰጥቷል፡፡

“የኦሮሞ ገበሬዎችን በዘዴ ማፈናቀልና ግድያን ጨምሮ በተማሪዎች ላይ እየተወሰደ ያለው የኃይል እርምጃ ይቁም” ሲሉ የጠየቁ የኦሮሞ ተወላጅ የሆኑ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያ አሜሪካዊያን ዛሬ ዋሽንግተን ዲ.ሲ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ የተቃውሞ ሰልፍ አካሂደዋል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ የኢትዮጵያ መንግሥት ፀጥታ ኃይሎች እየወሰዱ ያሉት የጭካኔ የኃይል እርምጃ ነው ሲል የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቹ ሂዩማን ራይትስ ዋች አስታውቋል፡፡

የዋሽንግተን ዲ.ሲ ሜትሮፓሊታን የኦሮሞ ወጣቶች ቡድን ያዘጋጀውና የመራው ሰልፍ ነው በኢትዮጵያ ኤምባሲ ደጅ ላይ የተካሄደው፡፡

ሰልፈኞቹ “ኢትዮጵያ ውስጥ የተቃውሞ ድምፃቸውን እያሰሙ ካሉ ተማሪዎች ጎን እንቀማለን፤ የኦሮሞ ገበሬዎችን ማፈናቀልን፣ መንግሥት እያከናወነ ባለው ሥራ ላይ ትኩረት ስለሳቡ ጥቃት በተሠነዘረባቸው ተማሪዎች ላይ የተፈፀመውን ጅምላ ግድያ እንቃወማለን” ብለዋል፡፡

የኦሮሞ ወጣቶች ቡድኑ ከሰልፉ ጋር አያይዞ ያወጣው የፕሬስ መግለጫ “ሥጋታችንን እያሰማን ነው፤ ኢትዮጵያ ውስጥ እየተፈፀመ ያለውን ልቅ የሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ረገጣ፤ በተለይ በውጤቱ በአሥር ሺሆች የሚቆጠሩ የኦሮሞ ገበሬዎችን ከአዲስ አበባ አካባቢ ሊያፈናቅል የሚችለውን የመንግሥት ዕቅድ በሰላማዊ መንገድ በተቃወሙ ተማሪዎች ላይ የተፈፀመውን ግድያ እየተከታተሉ እንዲዘግቡና እንዲያጋልጡ ለመገናኛ ብዙኃን ጥሪያችንን እናቀርባለን” ይላል፡፡  

በኤምባሲው ደጅ ላይ የተካሄደውን በተመለከተ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ፐብሊክ ዲፕሎማሲና የኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊው አቶ ዋህደ በላይ በተፈጠረው ሁኔታ መንግሥት በእጅጉ ማዘኑን በይፋ መግለፁን ሕይወታቸው ለጠፋ ሰዎች ቤተሰቦችም ይህንኑ ማሳወቁን ገልፀዋል፡፡

የታሰሩት የድረገጽ ጸሐፍት የፍርድ ቤት ውሎ

የኢትዮጵያ ፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የአራዳ ምድብ ችሎት ፣ ፖሊስ ከ10 ቀናት በፊት በታሰሩት በ6 ድረገጽ ጸሐፍት ጉዳይ ላይ ዛሬ የጠየቀውን የ15 ቀናት የምርመራ ጊዜ ወደ 10 ቀናት ዝቅ አደርጓል።

Symbolbild Justitia Justizia
ከሰዓት በኋላ በዝግ በተካሄደው ችሎት ተከሳሾቹ ለመጀመሪያ ጊዜ ፍርድ ቤት ሲቀርቡ ከውጭ ኃይሎች ጋር በመተባበር ማህበራዊ ሚዲያዎችን በመጠቀም ትርምስ ለመፍጠር አሲረዋል ተብለው የተመሰረተባቸው ክስ ዛሬ ከሽብርተኝነት ጋር ተያይዞ መቅረቡን የተከሳሾቹ ጠበቃ ለዶቼቬለ አስታውቀዋል። በዚህ የተነሳም የዋስ መብት እንደተነፈጋቸው ጠበቃቸው ተናግረዋል።
የአዲስ አበባው ወኪላችን ዮሐንስ ገብረ እግዚዘብሔር አጭር ዘገባ ልኮልናል። በተያያዘ የፍርድ ቤት ዜናም፤ የኢትዮጵያ ፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 11ኛ ይግባኝ ሰሚ ፍትሃ ብሄር ችሎት ለአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የአመራር አባል ለአቶ አስራት ጣሴ ይግባኝ ብይን ለመስጠት ዛሬ ሌላ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጠ ። ፍርድ ቤቱ ዛሬ ለአቶ አስራት ይግባኝ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ነበር ። ሆኖም ዳኛው ምርመራውን አላጠናቀቅኩም ሲሉ ውሳኔ ለመሰጠት ለግንቦት 19 2006 ዓም ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠታቸውን የአዲስ አባባው ወኪላችን ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ዘግቧል።

http://www.dw.de/

Sunday, 4 May 2014

ለኦህዴድ ባለስልጣናትና አባላት; ለኦሮሚያ ፖሊስ አባላት፣ etc

From Qeerroo Oromia
ለኦህዴድ ባለስልጣናትና አባላት፣
ለኦሮሚያ ፖሊስ አባላት፣
ለኦሮሚያ አድማ በታኝ ፖሊስ አባላት፣
ለኦሮሚያ ማረሚያ ቤቶች ፖሊስ አባላት እንዲሁም
የፌዴራል ፖሊስ አባል ለሆናችሁ የኦሮሞ ልጆች እንዲሁም በወያኔ መከላከያ ሠራዊት ውስጥ ለሚትገኙ ወገኖች በሙሉ
እናንተስ ከየትኛው ወገን ናችሁ!?
ይህንን ወቅታዊና ታርካዊ ጥያቄ ትመልሱ ዘንድ ጊዜው ደረሰ። እናንተ የሚታገለግሉት አሸባር ቡድን ጠላትነቱን በገሃድ ባረጋገጠ መልኩ ህዝባችሁን በገዛ ሃገሩ ላይ በአልሞ ተኳሽ ነፍሰገዳዮች ጥይት ሲያስረሸን ከዓይናችሁ ኣልፎ የድፍን ዓለም መነጋገሪያ ሆኗል። ከዚህ ህዝባችሁ ላይ ከተቃጣ ወደር የለሽ የጂኖሳይድ ጭፍጨፋ ተሳታፊነት ራሳችሁን እንዲታቅቡ፤ እንዲሁም ይንን የዳግማዊ ነፍጠኞች ወረራን ለመቀልበስ ይቻል ዘንድ ከህዝባችሁ ጎን በመሆን ሰልፋችሁን እንዲታስተካክሉ ታሪካዊ ጥሪ ቀርቦላችኋል።
ከዚህ በፊትም በህዝባችሁ ላይ ስደረግ የነበረውን መሰል ጭፍጨፋና ፈርጀ ብዙ ጭቆና ተባባሪ እንዳትሆኑ ፣ ከተቻለ ደግሞ ከህዝባችሁ ፍላጎት ኣንጻር እንዲትሰለፉ ህዝባችሁ ተመሳሳይ ጥሪዎችን ስያቀርብላችሁ መቆየቱ ይታወሳል። ሆኖም ግን በወቅቱ ለዚህ ሕዝባዊ ጥሪ አዎንታዊ ምላሽ ባለመስጠታችሁ ይባስ ብሎም ተሳታፊ ሆኖ በመገኘታችሁ የኦሮሞ ህዝብ ለአሳቃቂ እልቂት ተዳርጓል።
ይህ ተደጋጋሚ ጭፍጨፋና ጭቆና የበዛበት ህዝብ ራሱን ለመከላከልና ብሔራዊ ነፃነቱን ለመጎናጸፍ ያለዉን ብቸኛ መንገድን በህይዋቱ ቤዛ ተያይዞታል።
ታላቁ የኦሮሞ ህዝብ በዳግማዊ ነፍጠኛ ኃይሎች እየደረሰበት ያለውን አሰቃቂ ጥቃት በመመከት ለትግሉ ያለውን ጽናት ና ቁርጠኛነት በውል አራጋግጧል። ይህ ህዝባዊ ንቅናቄ ለመጨረሻ ግቡ እስኪ በቃ ድረስ አጠቃላይ ሕዝባዊ ኃይሉን በማቀናጀት በተጠናከረ መልኩ እንዲቀጥል ለህዋታቸው ሳይሳሱ የሚተጉ ኣእላፍ የቁርጥ ቀን ልጆቹን ኣሰልፏል።
በመሆኑም ከላይ በተጠቀሰዉ መዋቅር ዉስጥ የሚትገኙ የኦሮሞ ልጆች፣ በተለይ ደግሞ የወታደራዊና ፖሊሲ አባላት ለሆናችሁ ታጣቂ ኃይሎች ህዝባችሁን የማዳን ብሔራዊ ግዴታን ትወጡ ዘንድ እነሆ ይህ ታሪካዊ ጥሪ በዲጋሚ ቀርቦላችኋል። ስለዚህ በመፍረስ ላይ የሚገኘውን አሸባሪ ሥርዓት በመልቀቅ ለዚህ ብሔራዊ ጥሪ ፈጣንና ተግባራዊ ምላሽ በመስጠት ራሣችሁን ከተጠያቂነት እንዲታድኑ ይሁን!
ዘለዓለማዊ ክብር ለተሰው ንጹሃን የኦሮሞ ተማሪዎች!!

Qeerroo Oromia    

Saturday, 3 May 2014

ኦሮሚያ ካለቀሰች በኋላ – ህዝብ ሃሳቡን ሊጠየቅ ነው

የኢህአዴግ ቴሌቪዥን የቅስቀሳ ዘመቻ ጀመረ

mothers


በአምቦ ህዝብ አዝኗል። የሟቾች ቁጥር ከ22 በላይ እንደሆነ ይገመታል። በድፍን ኦሮሚያ ከ36 ሰዎች በላይ ተገድለዋል የሚሉ መረጃዎች አሉ። ኢህአዴግ ባወጣው መግለጫ 11 ሰዎች መሞታቸውን አምኗል። ታዛቢዎች እንደሚሉት ኦሮሚያ እያነባች ነው። ህዝብ ለቅሶ ከተቀመጠ በኋላ ኢህአዴግ በቴሌቪዥን ቅስቀሳ ጀመረ።
አርብ ሚያዚያ 24፤2006 (2/05/2014) ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም በትዊተር ባሰራጩት መረጃ በጉዳዩ ዙሪያ ህዝብ ሃሳቡን እንደሚጠየቅ አመላክተዋል። የዚሁ መነሻ እንደሆነ የተነገረለት የቅስቀሳ ዘመቻ ዛሬ በቴሌቪዥን ተላልፏል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ አቶ ኩማ የድንበር ጉዳይ እንደማይነሳ በመጥቀስ ተቃዋሚዎችን ወቅሰዋል።

Friday, 2 May 2014

ሰበር ዜና- የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ (ኢጋመ) ፕሬዝደንት ጋዜጠኛ በትረ ያቆብ ተሰደደ

May 2, 2014

Journalist Betre Yakobከሳምንት በፊት የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ ፕሬዝዳንትና ምክትል ፕሬዝዳንት በአፍሪካ ህብረት ጋባዥነት የኢትዮጵያን ችግርና አፈና በተለይ በሚዲያው ላይ ያለውን ጫና እና ጋዜጠኞች ላይ የሚደርሰውን አፈና ለመግለጽ ወደ አንጎላ አቅንተው ነበር፡፡ በጉዳዩ ላይ ሰፊ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ለአፍካ ህብረትም የመፍትሄ ሀሳብ ማቅረቡና ለሰብአዊ መብት ኮሚሽነሩም መልስ መስጠቱ ይታወቃል፡፡
ጋዜጠኛ በትረ ያቆብ ስብሰባው ከተጠናቀቀ በኋላ ወደ አገሩ ለመመለስ በሚዘጋጅበት ወቅት የዓለም አቀፍ የጋዜጠኛ ማህበራትን ጨምሮ ሌሎች የዓለም አቀፍ ተቋማት ሳይቀሩ እሱን ለማሰር የተደረገው ዝግጅት በተጨባጭ ማስረጃ ስላቀረቡለት መሰደዱን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገልጸዋል፡፡ የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎች በታሰሩበት ወቅት ፖሊስ የበትረ ያቆብን ቤት በመፈተሸ ያገኘውን ወረቀት ሁሉ እንደወሰደም ምንጮቻችን ጨምረው ገልጸዋል፡፡
ጋዜጠኛ በትረ ያቆብ አንጎላ በተደረገው የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ኮሚሽነሩን በግል እንዳገኛቸውና ኮሚሽነሩም በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጡ በመግለጽ እንዲሚያገኙት ቃል ገብተውለት እንደነበር ተገልጿል፡፡ በተጨማም ከበርካታ የአፍሪካ ህብረት ባለስልጣናት ጋር ስለ ኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታና በሚዲያው ላይ ስለሚደረገው ጫና የተወያዩ ሲሆን አብዛኛዎቹ በተለያዩ መንገዶች እገዛ ለማድረግ ቃል ገብተውለት እንደነበር ከታማኝ ምንጮች ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ በስብሰባው ወቅት ኢትዮጵያንና የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክን ወቅታዊ ሁኔታ የሚገልጹ ጽሁፎች ለተሰብሰብሳቢዎቹ ተበትነዋል፡፡

Thursday, 1 May 2014

በኦሮሚያ ግጭቶች ሕይወት ጠፋ

በአዲስ አበባ ዙሪያ ያሉ ከተሞችን በዋና ከተማይቱ ማስተር ፕላን ውስጥ አካትቶ ለማልማት በሚል የተያዘውን ዕቅድ ከተቃወሙ የኦሮሚያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ጋር በተነሣ ግጭት በሰው ይወትና ንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን የመንግሥት ኮመዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት አስታወቀ፡፡


ፅ/ቤቱ ሐሙስ፣ ሚያዝያ 23/2006 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ በመዳ ወላቡ የሦስት ተማሪዎች፣ በአምቦና ቶኬኩታዮ ከተሞች የሰባት ሰዎች ሕይወት ማለፉንና በቢዝነስና ኮንስትራሽን ባንክ ላይ የዘረፋ ሙከራ መደረጉን ገልጿል፡፡

በሃረማያ ማንነታቸው ባልታወቀ ሰዎች በተወረወረ ፈንጂ የአንድ ተማሪ ሕይወት ማለፉንና ሌሎች ሰባ ተማሪዎች መቁሰላቸውን ፅ/ቤቱ በዚሁ መግለጫው አስታውቋል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ በአምቦና አካባቢዋ “ቁጥራቸው 17 የሚደርስ ሰዎች ተገድለዋል” ሲል የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ - ኦፌኮ ከስሷል፡፡
ኦፌኮ የአካባቢውን ምንጮች ጠቅሶ ባወጣው መግለጫ “የኢሕአዴግ መንግሥት ለዚህ የኃይል እርምጃ ተጠያቂ ነው” ብሏል፡፡

መግለጫው አክሎም “የኦሮሞና የአማራ ብሔረሰቦችን ለማጋጨትም ደባ እየተካሄደ ነው” ብሏል፡፡

http://amharic.voanews.com/

Ethiopia: Government Massacre in Ambo Feared to have claimed 20 Lives

Ethiopian college student gunned down by government forces in Ambo, Ethiopia - 1 May 2014
14 years old student gunned down by Ethiopian government forces in  Oromia- 1 May 2014

Death at from Yesterday’s massacre in Ambo feared to have been as high as 20 and in Robe (Bale) 3 death is reported. Addis Ababa University students stage protest ( picture below). At Haromaya University an explosion took place wounding scores of students watching soccer game; death reported but number unconfirmed. Dire Dawa University-about 300 students are said have been taken to jail. Heavy police and military presence across college campuses and city centers across the country

http://ayyaantuu.com/