Sunday 29 June 2014

ኢትዮጵያዊው-ኖርዌጂያን ኦኬሎ ኦካይ ኦቻላ ”ሞት ሊበየንበት ይችላል” -በሽብርተኝነት ክስ ሞት ተፈርዶባቸው ሞታቸውን የሚጠባበቁ 127 ሰዎች ኣሉ

በኖርዌይ ሃገር ውስጥ በኖርዌጂያንኛ የሚታተመው ዳግብላደት የተባለው ጋዜጣና ድረ-ገጽ ”ኢትዮጵያዊው-ኖርዌጂያን” ኦኬሎ ኦካይ ኦቻላ በሚቀጥለው ሳምንት ሞት ሊበየንበት ይችላል” ሲል ኣውጥቶኣል።

”ባለፈው ሳምንት ለማወቅ እንደተቻለው ዕድሜው 52  የሆነና  ኦኬሎ ኦካይ ኦቻ  የተባለ ኖርዌጂያን ኢትዮጵያ ውስጥ በሽብርተኝነት ተከሶ በእስር ላይ ይገኛል።” tiltalt for terror በማለት የጀመረው የኖርዌዩ ዳግብላደት ሲቀጥልም…”የኢትዮጵያ መንግስት ቃለ ኣቀባይ እንደሚለው ገንዘብ ኣሰባስቦና ኣጥቂ ቡድን መልምሎ ኣደጋ ለማድረስ ሲሞክር ያዝነው በማለት መከሰሱን ያትትና በበኩላቸው የኖርዌዩ የሰብኣዊ መብት ጥበቃም ሆኑ የዓለም ኣቀፉ ሰብኣዊ መብት ተሟጋቾች ድርጊቱን በጥብቅ ያወገዙት ሲሆን፣ ኣያይዘውም ለዚሁ ድረ-ገጽ ታሳሪው ግለሰብ ያለበት ሁኔታ ከወትሮው የከፋ እንደሆነም ስጋታቸውን እንደገለጹለት ያወሳል።
 ኢትዮጵያንም ሆነ የቀድሞው የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት፣ በኣሁኑ ወቅት በማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ውስጥ የሚገኙትን  ኦኬሎ ኦካይ ኦቻ ”በሚገባ ያውቃሉ” ያሉዋቸውን የሰብኣዊ መብት ተሟጋችና ኖርዌጂያን ፈሊክስ ሆርነ ን  ኣነጋግሮ ድረ-ገጹ ያገኘው መልስ ”ኖርዌጂያኑን ኦኬሎ በሚቀጥለው ሳምንት የሚሰየመው ችሎት ሞት ሊበይንበት ይችላል” በማለት የገለጹ ሲሆን ኣክለውም፣
”በሃገሪቷ ውስጥ በሽብር ወንጀል የሚከሰሱት ዜጎች የሚገጥማቸው የሞት ፍርድ ነው። ነገር ግን እነዚህ ሞት የሚፈረድባቸው ዜጎች ምንም ማስረጃ ያልቀረበባቸው ናቸው። በሽብር ክስ ስለተከሰሱ ብቻ ዕድላቸው ይሄው ነው። በሞት ቀጠና የሚገኙትን ዜጎች የሚዘግበው ዓለም ኣቀፉ ድርጅት በኢትዮጵያ በእስር ቤት ውስጥ በሞት ቀጠና (ሴል) የሚሰቀሉበትን ወይም የሚገደሉበትን ጊዜ የሚጠባበቁ 127  ዜጎች  ይገኛሉ ሲል ፈሊክስ ሆርነ ለድረ- ገጹ ገልጸዋል።

Declaration of Unity of the OLF


Aasxaa ABO-8.25.13June 28, 2014 (Oromo Liberation Front) — It is with great pleasure that we announce to our people and the supporters of our struggle for freedom the good news that, based on the accord they made in Kampala, Uganda, in November 2012, the two organizations of the Oromo Liberation Front (OLF) known as OLF Shanee Gumii (”OLF National Council”) and OLF Qaama Ce’umsaa (”OLF Transitional Authority”) have resolved our differences and agreed to combine our two leaderships, unify our members, merge our organizational structures and inaugurate a reunified OLF. Although OLF has encountered many obstacles during the last forty years, there was no time when it has stopped the struggle that it was established to lead. No one can deny the fact that the national struggle led by the OLF has scored many victories and made many significant achievements that have taken the Oromo people a long way toward the national goal of independence. Among these great achievements is the level of political awareness of our people.
At the same time, we witness that the Oromo people are being targeted for extinction more than any time before. Oppression has reached intolerable levels making our people to rise up in defiance of tyranny, protesting peacefully in all corners of Oromia. But, as witnessed in the killings of students and others in many places in Oromia, the TPLF regime is responding violently to their lawful demands. Defying enemy atrocities, imprisonment, and torture the young Oromo generation are making it known to the world that they will not tolerate humiliation and oppression anymore and that they will make the necessary sacrifices to liberate their people and homeland from alien oppressors. The OLF extends its condolences to families who lost their beloved sons daughters and expresses its admiration for the courage and bravery they have shown by the young Oromo generation to defend their people’s legitimate rights. As the vanguard of the Oromo struggle for freedom, we re-iterate our determination to continue the struggle until our people become masters of their destiny.

Saturday 28 June 2014

የኦሮምያ ክልል ራዲዮና ቴሌቪዥን ጋዜጠኞች አባረረ

ሰኔ ፲፱(አስራ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በተለያዩ የስራ ዘርፎች ተሰማርተው ሲሰሩ የነበሩ 17 ጋዜጠኞች ከስራ መባረራቸው ተገልጾላቸዋል።

ጋዜጠኞች የተባረሩበት ዝርዝር ምክንያት ባይታወቅም፣ ከአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ጋር በተያያዘ ከተፈጠረው ተቃውሞ እንዲሁም ባህርዳር ላይ ተደርጎ ከነበረው የስፖርት ዝግጅት የቀጥታ ስርጭት ጋር በተያያዘ ሳይሆን አይቀርም።
ቀድም ብሎ ውስጣዊ ግምገማዎች ሲካሄዱ እንደነበር የኢሳት የመረጃ ምንጮች ጠቁመው፣ 6 የሚሆኑ ጋዜጠኞች ቀደም ብለው እንዲታገዱ መደረጉን አስታውሰዋል።
በውስጥ ትርምስ ውስጥ የሚገኘው ኦህዴድ፣ በክልሉ የሚታየውን አለመረጋጋት ለማብረድ ላይ ታች ቢልም እስካሁን አልተሳካለትም።
በሚቀጥሉት ተከታታይ ሳምንታት አንዳንድ የዞን እና የወረዳ ባለስልጣናት እንደሚባረሩ የኢሳት ምንጮች ጠቁመዋል።

Friday 27 June 2014

Aid donors announce investigation into tribal evictions in Ethiopia

Bulldozers clearing Mursi land in Mago National Park, where communities are being evicted from their land to make way for sugar plantations
Bulldozers clearing Mursi land in Mago National Park, where communities are being evicted from their land to make way for sugar plantations
June 24, 2014 (Survival International) — Representatives of some of Ethiopia’s biggest aid donors have announced that they will send a team to the southwest of the country to investigate persistent reports of human rights abuses amongst the tribes living there.
Survival International, the global movement for tribal peoples’ rights, has exposed how the tribal people of the Lower Omo Valley are being persecuted and harassed to force them off their land to make way for cotton, oil palm and sugar cane plantations.
Many other organizations have published similar reports.
The plantations are made possible by the Gibe III hydroelectric dam, which is itself the subject of huge controversy.
The dam, which is nearing completion, will have a serious impact on the livelihoods of 500,000 tribal people, including those living around Kenya’s Lake Turkana.
It is also projected to have catastrophic environmental consequences for the region, which is hometo renowned UNESCO World Heritage sites on both sides of the border.
Survival and other NGOs have repeatedly denounced the eviction of hundreds of Bodi and Kwegu and continue to receive reports that people are being intimidated into leaving their lands for resettlement camps.

ያልተፈታው የሰኔ ቋጠሮ! (The Ethio-Eritrean War and the Role of Meles, By Mahder Jeganu)


እንደሚታወቀው የኢትዮ – ኤርትራ ጦርነት በሁለቱም አገሮች ከባድ የሚባል መስዋእትነት ተከፍሎበታል። ይህ ጦርነት ሲጀመር ምክንያቱ ምን ነበር? ለመንስ ተደረገ? መቸና ለመን እንዲቆም ተደረገ? በግዜው ጦርነቱ ሲጀመር አንዳንድ የፖለቲካ ተንታኞችና ኢህአዴግ እንዳሉት ከሆነ የኤርትራ መንግስት ኢኮኖሚያዊ ችግር ነው ይላሉ። እውነቱ ይሀ ከሆነ ሆድ ይፍጀው። ለማነኛው ዛሬ ድረስ የእነዛን ጥያቄዎች መልስ ሳይፈታ ይሀው 16 ዓመታት አልፎ ቋጠሮውን ሳይፈታ ቀርቷል።
የሻዕቢያ ወረራ ገና ከመፈፀሙ በ1990 ዓ/ም በኤርትራ ይደረጉ የነበሩት ዝግጅቶችና ግልፅ የሆኑ የወረራ እቅዶች እንመልከት
1. ሻዕቢያ መጀመሪያ የመን ከዛ ሱዳንና ጅቡቲን በጦርነት መነካካት ከጀመረች ሰነባበታለች። በዚህ ግዜ በአካባቢው ከነበሩት አገራት የቀራት አንድ ኢትዮጵያ መንካት ብቻ ነበረ።
2. በኤርትራ የተለያዩ አገራዊ አጀንዳዎች ተነስተው ከኢትዮጵያ ጋር እያነፃፀሩ አስተያየትና ሃሳብ በግልፅ መስጠት የጀመሩት በመጋቢት 1990 ዓ/ም ነበር። በዛን ወቅት በተለይ በእምባ ትካላ በተባለው ቦታ ከሻለቃ አመራር በላይ በአጀንዳው እንዲወያዩበት ተደርጓዋል። በወቅቱ ኤርትራ በ 5 ኮር የተደራጀ ጦር አዘጋጅታ ነበር።
3. ሚያዝያ 29/1990 ዓ/ም ጀኔራል ስብሃት ኤፍሬም የኢትዮጵያ ሰራዊት ሁኔታ የሚገልፅ ደብዳቤ ለሁሉም የሻዕቢያ ክፍሎጦሮች በመላክ እንዲዘጋጁበት መልዕክት አስተላልፈዋል። በደብዳቤው የሚታይው መረጃ ኢትዮጵያ 30,000 ተዋጊ 20,000 እስታፍ ብቻ እንዳላት የሚገልፅ እስታቲክስ ጭምር ነበረበት።
4. ሻዕቢያ የተለያዩ ወታደራዊ መኪኖችንና ታንኮች ለጥገና በማስገባት አሉ የሚባሉ ሰዎች ከኢትዮጵያ ሳይቀር የቀድሞ የደርግ እውቁ የታንክ ባለሞያ ኮነሬል ተስፋማርያም ሳይቀር ጠርቶ ታንኮችንና ተሽከርካሪዎችን ማዘጋጀት የጀመረወ በዚሁ አመት 1990 ዓ/ም ነበር።

Tuesday 24 June 2014

ሱዳን ውስጥ ስቅላት ተፈርዶባት የነበረችው ሜርያም ተለቀቀች

በሱዳን ሻሪዓ መሠረት ሃይማኖቷን ወደ እሥልምና እንድትቀይር ታዛ እምቢ በማለቷ እንድትሰቀል ተፈርዶባት የነበረችው የክርስትና ዕምነት ተከታይ ሴት ከእሥር ከተፈታች በኋላ እንደገና በቁጥጥር ሥር ውላ እንደገና ተለቅቃለች፡፡


በሱዳን ሻሪዓ መሠረት ሃይማኖቷን ወደ እሥልምና እንድትቀይር ታዛ እምቢ በማለቷ እንድትሰቀል ተፈርዶባት የነበረችው የክርስትና ዕምነት ተከታይ ሴት ከእሥር ከተፈታች በኋላ እንደገና በቁጥጥር ሥር ውላ እንደገና ተለቅቃለች፡፡

ሚሪያምና ቤተሰቧ በቁጥጥር ሥር ውለው የነበረው ኻርቱም አይሮፕላን ጣቢያ ላይ የነበረ ሲሆን የሱዳን አሜሪካዊ ባለቤት የሆነችው ሜሪያም ኢብራሂም በቅርቡ ወደ ዩናይትድ ስቴትስ ልትጓዝ እንደምትችል አንድ አሜሪካዊ የሕግ ባለሙያ ጠቁመው ነበር፡፡

አይሮፕላን ጣቢያው ላይ ተይዘው የቆዩት ለሰዓታት መሆኑንና የተያዙትም ከመጓጓዣ ሠነዶቻቸው ጋር ለማጣራት እንጂ እሥራት አልነበረም ሲሉ የሱዳን ባለሥልጣናት የገለፁለት መሆኑን የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

ቤተሰቡ ከሱዳን በሰላም እንዲወጣ ለማድረግ እየሠራ መሆኑንም ኻርቱም የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ አስታውቋል፡፡
http://amharic.voanews.com

ሰበር ዜና ጅዳ ሳውዲ አረቢያ አንዲት ኢትየጵያዊት በጅዳ ቆንስል ግቢ ታንቃ ተገኘች

June23/2014


በሳውዲ አረቢያ ጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት ግዜያዊ የስደተኞች መጠለያ ውስጥ እንዲት ኢትዮጵያዊት ታንቃ መገኘቷ የአካቢውን ማህበረሰብ ደረት ሲያስደቃ መዋሉን ቦታው ላይ የነበሩ የአይን እማኞች አረጋግጠዋል። ዛሬ በኢትዮጵያ ሰአት አቋ ጣጠር ከቀኑ 10 ሰአት ቆንስላው ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ ታንቃ የተገኘቸው ወጣት በ 20 አመት የእድሜ ክልል ውስጥ የምትገኝ መሆኗን የሚናገሩ እማኞች በኮንተራት ለስራ መጥታ ከአሰሪዎቾ ባለመስማቷ በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ ግዜያዊ መጠለያ ኮንቴነር ውስጥ ለረዥም ወራት ስትሰቃይ የኖረች ሳትሆን እንደማትቀር ይናገራሉ ; ፡ በኢትዮጵያ ሰዓት አቋጣጠር ዛሬ ከቀኑ 10 አካባቢ እዚህ ቆንስላ ግቢ ውስጥ የታነቀቸውን ወጣት በአይናቸው ለማየት እድል ያገኙ እማኞች ወጣቷ እራሷን አንቃ ለመግደል ስትወራጭ አንገቷ ውስጥ የገባው ገመድ መስል ነገር ጉሮሮዋን ቆርጧ ወዲያው ሳይገድላት እንዳልቀረ ይገልጻሉ።

ይህ ዜና እስከ ተጠናከረበት ግዜ ድረስ የወጣቷ ሬሳ አለመንሳቱን የሚናገሩ ምንጮች በአካባቢው የፓስፖርተ እድሳት እና መስል ተዘማጅ ጉዳዩቹን ለማስፈጸም የቆንስላ ግቢውን አጨናነቀው እምባ ሲራጭ የነበሩ ኢትዮጵያውያን ከቆንስላው ጽ/ቤት እንዲወጡ መደረጋቸውን የአይን እማኞቹ አክለው ገልጸዋል ። ይህ በዚህ እንዳለ የሬሳ ጉዳይ የሚከታተለው እና የቀድሞ የኮሚኒቲ አመራር አቶ መሃመድ ሸህ ተፈቅዶለት ወደ ግቢው ሲገባ ያዩ ምንጮች ቦታው ላይ የሳውዲ ፖሊሶች እና ዲፕሎማቶች መገኘታቸውን አረጋግጠዋል ። የጅዳ ቆንስ ጽ/ቤት የእህቶቻችንን አስከሬን ሲያስተናገድ የመጀመሪያ ግዜው እንዳለሆነ የሚናገሩ ወገኖች በዲፕሎማቱ የአሰራር ድክመት በአንድ ወር ውስጥ ብቻ ለሁለተኛ ግዜ ታንቃ ህይወቷ ባለፈው ወጣት ተደናግጠው ሲጮጮሁ በነበሩ ኢትዮጵያውያን የቆንስላው ጽ/ቤት ድባብ ወደ መቃብር ስፍራ ነት ተለውጦ ማምሸቱን ይናገራሉ ።

በአሁኑ ግዜ በዚህ የቆንስላ ቅጥር ግቢውስጥ ከ 40 የሚበልጡ ተፈናቃይ የኮንተራት ሰራተኞች ከሰው እይታ ተገለው ይሚገኙ ሲሆን ባዶ ክፍሉ ውስጥ ያለምንም እርዳታ ሃገር ትገባላቹ በሚል ተስፋ መጋዘን ተቆልፎባቸው ለበለጠ ስቃይ እና መከራ እይተዳረጉ ከሚገኙ እህቶቻን መሃከል አብዛኛዎቹ የፈላ ውሃ በአሰሪዎቻቸው የተደፋባቸው የተድፈሩ እና ደሞዛቸው የተነጠቀ መሆኑ ይነገራል።፡፤ የወገኖቻችን ሞት ከሚፈበረከበት ሁለተኛው ማዕከል ጅዳ ከሆነው የ ቆንስላ ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ በአንድ ወቅት አንድ የውሃ ጉድ ጓድ ውስጥ ሬሳዎ በተገኘ ኢትዮጵያዊት ጉዳይ የህ.ወ.ህ.ቱ አባል አቶ ገሬ ለወራት ወህኒ ቢወርዱም የሞቾ ምስኪን ጉዳይ ተድበስብሷ ሲቀር አቶ ገሬ ከወራት እስራት በኋላ በወጭ ጉዳይ ግፊት መፈታታቸው በህዝብ ዘንድ ተቃውሞ ማስነሳቱ አይዘነጋም።
Ethiopian Hagere ጅዳ በዋዲ

ጄኔራል ሰዓረና ጋዜጠኛ እስክንድር (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

ሰኔ 1 ቀን 1997ዓ.ም፤ በአዲስ ከተማ ት/ቤት የተጀመረው ተማሪዎችንና ንጹሃን ዜጐችን በግፍ የመግደል እርምጃ ተከትሎ አብዛኛው ባለስልጣናት ልጆቻቸውን ከየት/ቤቱ በአጃቢ ያስወጡ ነበር። ወደ ካቴድራል ት/ቤት በሁለት ኮብራ ተጭነው የተላኩ 20 ልዩ የፌዴራል ፖሊሶች የጄ/ል ሰአረና የጄ/ል ብርሃነ (ወዲ መድህን) ሴት ልጆችን አጅበው ሄዱ። ሁለቱ ሴት ልጆች በማግስቱ አሜሪካ ኤምባሲ ቪዛ ተመቶላቸው ዓርብ ሰኔ 3 ቀን በረሩ። የብዙ ባለስልጣናት ልጆች በተመሳሳይ እንዲወጡ ተደረገ። ..29ሺህ የአሜሪካ ዶላር በተርም እየተከፈለላቸው መማር ቀጠሉ። የአዜብ ልጅና የእህቷ ልጅ፣ (በነገራችን ላይ አርአያ መኮንን ይባላል፤ በ1995ዓ.ም ቦሌ ከሩዋንዳ ፊት ለፊት ጥቂት ገባ ብሎ አዜብ ለዚህ ወጣት በ7 ሚሊዮን ብር ቪላ ቤት ገዝታ በስጦታ አበርክታለች። የቪላው ኪራይ ሂሳብ በስሙ ባንክ ይገባለታል) ..የአርከበና ስብሃት ልጆች በቨርጂኒያ፣ የሽፈራው ጃርሶ ልጆች በካሊፎርኒያ፣ የፖሊስ ኮሚሽነር የነበረው ወንጀለኛውና 5ሚሊዮን ዶላር ሰርቆ የወጣው ተስፋዬ መረሳ ልጆች በኒዮዎርክ….ወዘተ በተቀማጠለ ኑሮና በውድ ክፍያ መማር ያዙ። ባለፈው አመት በነርስ የተመረቀችው የጄ/ል ሰአረ ልጅ ሐመልማል ሰዓረ የምርቃት ፕሮግራም ላይ ጄኔራሉ ተገኝተው ነበር።…ወደ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እንለፍ።

Eskinder Nega's son Nafkot
እስክንድር በላባቸው ሰርተው ሃብት ካፈሩ ጥሩ ቤተሰቦች የተገኘ ልጅ ሲሆን የተማረው በሳንፎርድ ት/ቤት ነው። ከዚያም አሜሪካ መጥቶ ትምህርትና ህይወቱን ቀጠለ። “አገር አማን” ብሎ በዘመነ ኢህአዴግ አገር ቤት ገባ። ተደጋጋሚ እስርና ድብደባዎችን አሳለፈ። እነሆ “አሸባሪ” ተብሎ ከሌሎች ንፁሃን ጋር በእስር እየማቀቀ ይገኛል። እነ ጄ/ል ሰአረና መሰሎቻቸው በመቶ ሺህ በሚቆጠር ዶላር ልጆቻቸውን በአሜሪካና አውሮፓ ሲያስተምሩና ሲያንደላቅቁ፣ እንዲሁም ልጆቻቸውን ለማስመረቅ ሲገኙና ሲደሰቱ በአንፃሩ በመፃፉና ሃሳቡን በመግለፁ ብቻ እስር ቤት የተወረወረውና ናፍቆት ልጁን እንዳያሳድግ የተደረገው እስክንድር ነጋ ጭራሽ ቤተሰቡ ያወረሱትን ቤት በግፍ እንዲነጠቅ ተደረገ። በጄኔራሎቹና ባለስልጣናቱ ሰፈር ግን በሚሊዮን ብር የተገነባ ቪላ፣ ልጆቻቸው የሚንደላቀቁበት በመቶ ሺህ የሚቆጠር ዶላር…ወዘተ አለ። ይህ ከህዝብ የተዘረፈ የአገር ሃብት ነው!! የጄ/ል ሰዓረ ባለቤት ኰ/ል ፅጌ በስማቸው በገርጂ የተገነባውና ሰባት ሚሊዮን ብር የፈጀው ቪላ ሲገኝ የሚገርመው የቅጥር ግቢው ወለል በእምነበረድ መሸፈኑ ነው።
ሌላው በሙስና የታሰሩት የደህንነት ሹሞቹ ወ/ስላሴና ገ/ዋህድ..መኖሪያ ቤት ውስጥ በርካታ የጦር መሳሪያዎችና ቦንቦች እንዲሁም በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብና የቤት ካርታ ወዘተ መገኘቱን ገዢው ፓርቲ ይፋ አድርጓል። ዛሬ ጠያቂ ባይኖርም ቅሉ ነገር ግን ጄኔራሎቹና ባለስልጣናቱ እንደነ ወ/ስላሴ ዘርፈው ያካበቱት ለመሆኑ አያጠያይቅም።
የሚገርመው መፅሐፍትና ጋዜጣ የተገኘበት የእስክንድር ቤት ሲወረስ በአንፃሩ ህገ ወጥ የጦር መሳሪያና ሚሊዮኖች ተገኘበት ያሉትን የዘራፊዎቹን የሙስና ቤት አልነኩም።… እንደ እስክንድር ሁሉ አቶ አንዱአለም፣ አቶ በቀለ፣ ውብሸት፣ የሙስሊሙ ህብረተሰብ ተወካዮች እነ አቡበከር.. በሙሉ ልጆቻቸውን እንዳያሳድጉ የተደረጉ የህሊና እስረኞች ናቸው!! እንዲሁም ጄ/ል ሰአረ በምሳሌነት ተጠቀሱ እንጂ የአብዛኛው ባለስልጣን ከዘረፋ የተገኘ ህይወት ተመሳሳይ ነው። የአንዳንዶቹ ባለስልጣናትና ልጆች የአሜሪካ ውሎና ኑሮ የሚያሳይ በፎቶ የተደገፈ ማስረጃ እንዳለ ሳልጠቁም አላልፍም።