በሺ የሚቆጠሩ አፍሪቃውያን ስደተኞች ፤ እሥራኤል ውስጥ መብታቸው እንዲከበር ትናንት ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ አድርገዋል ፤ እንዲሁም ዛሬ ቴል አቪብ ውስጥ
ከምዕራባውያን ኤምባሲዎች ፊት ለፊት በመሰለፍ ፣ እሥራኤል ፤ ባወጣቸው አዲስ ህግ በረሃ ውስጥ ይዛ ያሠረቻቸው ባልደረቦቻቸው እንዲፈቱላቸው ያደርጉ ዘንድ መጠየቃቸው ተመልክቷል ። በአሥራኤል ባጠቃላይ ፤ 60 ሺ ያህል አፍሪቃውያን ስደተኞች እንደሚገኙ ይነገራል። እሥራኤል እነዚህን ሰዎች ህገ ወጥ ሥራ ፈላጊዎች ናቸው ትላለች፤ የሰብአዊ መብት ድርጅቶች ደግሞ ስደተኞች መሆናቸውን ነው የሚገልጹት።
No comments:
Post a Comment